November 7, 2018
3 mins read

በከንባታ ጠንባሮ ዞን ተቃውሞ ያነሱ ወገኖች ወደ አዲስ አበባ እና አርባ ምንጭ የሚወስደውን መንገድ ዘጉ

92421

በደቡብ ክልል፤ ከከምባታ ጠምባሮ ዞን ወደ አዲስ አበባ የሚያቀናው መንገድ ዛሬ ዝግ ሆኖ ዋለ:: የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች ሕዝቦች ክልል መንግሥት ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ማገባደጃ ላይ በሐዋሳ ያከናወነው 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የወረዳ ጥያቄ ተነስቶ፤ ለተወሰኑ ቦታዎች ሲፈቀድ ለ እኛ አልተፈቀደም በሚል ነዋሪዎቹ ተቃውሟቸውን እንደጀመሩ የአካባቢው የዜና ምንጮች ይገልጻሉ::

በከባታ ጠንባሮ ዞን ባሉት 7 ከተሞች ውስጥ ትናንት እና እና ከትናንት በስቲያ ተቃውሞ ሰልፎች ሲካሄዱ የቆዩ መሆኑን የገለጹት ምንጮች በተለይም በከምባታ ጠምባሮ ዞን የወረዳ ጥያቄ ያነሳችው አዲሎ ቀበሌ ትናንት፣ በጠምባሮ ወረዳ ደግሞ ከትናንት በስትያ ሰልፍ ነበር ያሉት የዜና ምንጮች በዛሬው ዕለት ተቃውሞው ወደ መንገድ መሸጋገሩን አስረድተዋል:

በመሆኑም ጠምባሮ ከተማ ጠምባሮ ከተማ አስተዳደር እንዲሆን ጥያቄ ያቀረቡት ነዋሪዎች በአዲሎ ቀበሌ መንገዶች መዝጋታቸው እና ወደ አዲስ አበባ የሚያቀናው መንገድ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ አልተከፈተም:: ይህም ብቻም ሳይሆን ወደ አርባ ምንጭ የሚያሻግረው መንገድ ም በዛሬው ዕለት በተቃውሞ አቅራቢዎቹ ተዘግቷል::

ሦስተኛ ቀኑን በያዘው ተቃውሞ መንገዶች ቢዘጋጉም ምንም ዓይነት በሰውም ላይም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የሚገልጹት ምንጮች የፊታችን ቅዳሜ በመላው ከንባታና ጠንባሮ ዞን ከፍተኛ ተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑን ነግረውናል::

በደቡብ ኢትዮጵያ ከምባታ ጠምባሮ ዞን በተለያዩ ጊዜያት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁና ሥራ ያጡ ወገኖች ባለፈው ሳምንት በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ሲያቀርቡ በፖሊስ እንደተቀጠቀጡ ዘ-ሐበሻ ዘግቦ እንደነበር ይታወሳል::

https://www.youtube.com/watch?v=LCftg3owFj4&t=4s

92418
Previous Story

የአማራ እና የትግራይ ክልል በመግለጫ በመጎሻሸም ቀጥለዋል

92426
Next Story

ዶ/ር አብይ ከከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ጋር ተወያዩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop