November 1, 2018
2 mins read

ፓርላማው በሙስና/ሌብነት የተጠረጠሩ አባላቱን ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው

92288

(ዘ-ሐበሻ) ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ እርምጃ አልወሰዱም ተብለው ከሚተቹባቸው ምክንያቶች አንዱ በሌብነት የበሰበሱ ባለስልጣናት ላይ እርምጃ አለመወሰዳቸው ይጠቀሳል:: በሌብነት ተጨማልቀዋል ተብለው ከተጠረጠሩት መካከል ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስጣልን ከመጡ ወዲህ ስም ካላቸው ባለስልጣናት መካከል በሌብነት የተጥርጦ ባለፈው ሰኔ የታሰረው ሕወሓቱ የቀድሞ ኢንሳ ም/ዳይሬክተር ቢኒያም ተወልደ ሲሆን ሌሎች ባለስልጣናት ሳይነኩ መቅረታቸው አነጋጋሪ ሆኖ ቆይቷል::

በዚህም መሰረት ኢህአዴግ 100% የሚቆጣጠረው የተወካዮች ምክር ቤት በቀናት ውስጥ በሚያከናውነው ስብሰባው በከፍተኛ ሙስና የተጠረጠሩ አባላቱን ያለመከሰስ መብት እንደሚያነሳ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንዳሉት ያለመከሰስ መብታቸው ከሚነሳው ባለስልጣን የፓርላማው አባላት ውስጥ ውስጥ ባለፈው 27 አመታት በከፍተኛ ስልጣን ላይ የቆዩ ይገኙበታል፡፡

ዘ-ሐበሻ ከ3 ቀን በፊት በዜና እወጃው ፌዴራል ፖሊስና አቃቤ ሕግ በ33 ትላላቅ ኩባንያዎች ላይ ምርመራ እያደረገ መሆኑንና ከግማሽ በላይ የሆኑት ምርመራ መጠናቀቁ መዘገቡ ይታወሳል:: በዚህ ምርመራ ላይም ቢሊዮን ብሮች የሚቆጠሩ ወንጀሎችን እንዳገኘ ዘግበናል:: ይህ ምርመራ ያለመከሰሰ መብታቸው ከሚነሳባቸው ባለስልጣናት ጋር የሚያያዘው ነገር እንዳለ ዘ-ሐበሻ ምንጮቹን ጠይቆ በቂ ምላሽ ባያገኝም በምርመራው የበርካታ ባለስልጣናት እጆች እንደተጨማለቁ ገልጸውልናል::
https://www.youtube.com/watch?v=NaLy5pGAFTc

1 Comment

Comments are closed.

pexels nastya korenkova 8920170
Previous Story

Emily: Behind A Successful Journalist

92291
Next Story

የአዲስ አበባ ወጣቶች ክስ ወደሽብርተኝነት ተቀየረ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop