ኮለኔል አያናው መስፍን ቤተመንግስት ከሄዱት የወታደሮች ጀርባ አሉበት ተብለው ተጠርጥረው ታሰሩ

ከወራት በፊት ከአጋዚ ጦር ጋር የሚመሳሰል ‘ማበል ግብረሃይል’ የተባለ በዶ/ር ዓብይ አህመድ አማካኝነት እንዲቋቋም የተደረገ ሲሆን ከዚህ ከማበል ግብረሃይል አንዱ ሻምበል ወደ ቤተመንግስት ከነጠመንጃው መሄዱ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው የውስጥ መረጃ ይጠቁማል::

ከማበል ግብረሃይል በኮለኔል አያናው መስፍን ከበላይ ሆኖ የሚያዘውና ማዕረጋቸው ለጊዜው ማዕረጋቸው ያልተገለጸ ሞሲሳ እና በምክትሉ ፈቃዱ የሚመራው ሻምበል ጦር ወደ ቤተመንግስት በመሄዱ ከበስተጀርባው ያለው የደመወዝ ጥያቄ ሳይሆን ሌላ ነው በሚል ሦስቱም የክፍተኛ የጦር መኮንኖች ተጠርጥረው መታሰራቸውን የመከላከያ ምንጮች ገልጸዋል::

በቡራዩ የተከሰተውን ሁኔታ ለማርገብ ከአዋሳ የመጡት እነዚሁ ሞሲሳ እና ፈቃዱ የሚመሩት ሻምበል ጉዳይ አሁንም መነጋገሪያነቱ የቀጠለ ሲሆን በወታደሮቹ መሰረታዊ የደመወዝ ጥያቄ ጀርባ ሌሎች የተሴሩ ነገሮች ናቸው በሚል መከላከያው አሁንም እየታመሰ መሆኑ ታውቋል::

ለጊዜው የሶስቱ ከፍተኛ ጦር መኮንኖች ስም የመታሰራቸው ስም ይፋ ይሁን እንጂ በርካታ ሃላፊዎች እየታሰሩና
እየተገመገሙ ይገኛሉ::
_
https://www.youtube.com/watch?v=d1wWzuTMu2s

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ክልል መንግስት ተማሪዎችን ሰልፍ ከለከለ «ተማሪዎች ሰልፎች እንዳያደረጉ ለምን ተከለከሉ?» - ዓለምነው መኮንን

3 Comments

  1. Even though the procedur is wrong, the army will not do harm to this existing government,but the imbecils are trying to confuse the people.The Abashs are always suspishes and devilish thinkers.PLEASE STOP YOUR this dirty behaviour.thanks.

  2. Even though the procedur is wrong, the army will not do harm to this existing government,but the imbecils are trying to confuse the people.The Abashs are always suspishes and devilish thinkers.PLEASE STOP YOUR dirty behaviour,thanks.

  3. everything was on their hand to do what we fear but they did not have such ambition. God keeps those deserved to live. do not worry.

Comments are closed.

Share