የቀድሞው ብአዴን የአሁኑ አዴፓ በነበረከት ስምዖን ላይ ክስ ለመመስረት የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ አጠናቀቀ

አቶ በረከት ስምዖን እና ታደሰ ካሳ ጥንቅሹን በጥረት ኮርፖሬት ውስጥ በፈጸሙት ጥፋት በሚል ምክንያት ከድርጅቱ አግዶ በኋላም ከማዕከላዊ ኮሚቴነት ያባረረው አዴፓ በነዚህ እና በሌሎችም የጥረት ኮርፖሬሽን ባለስልጣናት ላይ ክስ ለመመስረት የመረጃ ማሰባሰብ ሥራውን ማጠናቀቁ ተሰማ::

የአማራ ክልል መንግስት ቃል አቀባይ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በስም አይጥቀሱ እንጂ “ከአሁን ቀደም የቀድሞው ብአዴን የአሁኑ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /አዴፓ/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥረት ኮርፖሬትን አስመልክቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን ማስተላለፉን እናስታውሳለን:: በውሳኔውም መሰረት ጥረት የለውጥ እርምጃዎችን ጀምሯል:: የጥረት አምራሮች ሰሞኑን በተቋሙ ውስጥ ብልሹ አሰራር የፈጸሙ አካላትን ለህግ ለማቅረብ የኦዲትና የመረጃ ማሰባሰብ ስራ ተጠናቋል::” ሲሉ ይፋ አድርገዋል::

“በተቋሙ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የአሰራር ግድፈት ሲፈጸምበት የቆየ በመሆኑ የባከነ ሐብትና የከሰሩ ኩባንያዎችም እንዳሉ ተለይቷል ::
ኮርፖሬቱ በበላይነት የሚያስተዳራቸው ከ20 ኩባንያዎችና ፕሮጀክቶች በላይ ቢኖሩም በውስጣቸው በነበረው ብልሹ አሰራር ምክኒያት ውጤታማ እንዳልነበሩ በግልፅ ታውቋል፡፡” ያሉት አቶ ንጉሡ ተቋሙን በአዲስ ለማደራጀት ከጥረት ዋና መስሪያ ቤት ጅምሮ በሁሉም ኩባንያዎችና ፕሮጀክቶች ላይ አዳዲስ አሰራሮችን ለመዘርጋት የሪፎርም ስራና በሰለጠነ ሰው ኃይል የማደራጀት ሥራ መጀመሩን ገልጸዋል::

እነበረከት ስምዖንን ብ አዴን ባወጣው መግለጫ በጥረት ኮርፖሬሽን ውስጥ ጥፋት በማጥፋት የተከሰሱ ቢሆንም ወዲያውኑ በሚዲያ ወጥተው ጥረትን ከወደቀበት አንስተው አትራፊ ድርጅት እንዳደረጉት; ምንም ጥፋት አለመፈጸማቸውን መግለጻቸው ይታወሳል:: አሁን አቶ ንጉሡ በለቀቁት መረጃ ለክስ የሚያበቃ መረጃ የተሰባሰበባቸውን ባለስልጣናት ስም ዝርዝር ባይጠቅሱም ድርጅቱ ቀደም ብሎ እነ በረከትን በጥፋት ተጠያቂ ማድረጉን የሚጠቅሱት ምንጮች መረጃው የተሰባሰበባቸው እነርሱው ናቸው ይላሉ::
እነ አቶ በረከት ስምዖን ኑሯቸውን ትግራይ ክልል ማድረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብርሀኑ ጁላ መልቀቂያ አስገባ | "መከላከያው ፈርሷል ተሸንፈናል" አበባው ታደሰ | “ከብዶናል” አረጋ ከፋኖ ጋር አስታርቁኝ | ኤርትራ ቁርጡን አሳወቀች ‹‹አሸማግሉን›› ጌታቸው፣

ጥረት ኮርፖሬት በስሩ የሚከተሉት 26 በስራ ላይ ያሉ እና በሒደት ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ያሉት ግዙፍ ተቋም ነው:: ያሉት አቶ ንጉሡ ድርጅቶቹን ዘርዝረዋቸዋል::

1. አምባሰል የንግድ ስራዎች ድርጅት
2. ዳሽን ቢራ ፋብሪካ
3. ዋሊያ ቆርኪ ፋብሪካ
4. ገንደ ውሃ የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ
5. ጎንደር ብቅል ፋብሪካ
6. ጣና ኮሙኒኬሽን የሞባይል መገጣጠሚያ
7. አዞላ ኤሌትሮኒክስ ፋብሪካ
8. ቲ ቲ እንጂኔሪንግ እና ማህበር
9. ላፓልማ ዳይቶማይት ፋብሪካ
10. ጀሪ የተፈጥሮ ምንጭ ውሀ ፋብሪካ
11.ተላጅ የልብስ ስፌት ፋብሪካ
12.የቆቦ ዶሮ እርባታ፤ እንስሳት ማድለብና ስጋ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ
13.ጣና ወረቀትና የወረቀት ውጤቶች ማምረቻ
14.ቢዲሲ ኮንስትራክሽን
15.ተከራርዋ የፕላስቲክ ማምረቻ
16. ዘለቀ እርሻ መካናይዜሽን
17.የዓሳ ልማት ፕሮጀክት
18. የትመን የጂፕሰምና የጅብሰም ውጤቶች ማምረቻ
19. ማዕድ የምግብ ኮምፕሌክስ ፕሮጀክት
20.ቲአይ ሜታልስ ፈርማንግ
21.የጁ ማርና የማር ውጤቶች ማምረቻ
22.የወተት ሀብት ልማት ማቀነባበሪያና የወተት ዱቄት ማምረቻ
23.ጥቁር አባይ ትራንስፖርት አ/ማ
24. እሸት ስታርችና የስታርች ውጤቶች ማምረቻ ፕሮጀክት
25. ጀርባ ፖኬጂንግ ፕሮጀክት
26.በለሳ የሎጂስቲክ አ.ማ
https://www.youtube.com/watch?v=dzVLCUTEMyY&t=3s

1 Comment

  1. Omg ! Berket Simon, is the most corrupted person and has to be investigated ! we know The UN and USA has zero tolerance for corruption and we call up on their involvement in this case as he is the most corrupted .If people like Bereket Simon is in power , how UN sustainable agenda of 2030 can be achieved.

    “The things speaks for itslef” his luxury life !!!

    https://en.wikipedia.org/wiki/Bereket_Simon

Comments are closed.

Share