ሲኖዶሱ የፓትርያርኩን ውሳኔ አስቀየረ

ቅዱስ ሲኖዶሱ በትናንትናው የስብሰባ ውሎው ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ በአብላጫ ድምጽ ወስኖባቸው የነበሩት የአዲስ አበባው ሊቀ ጳጳስ አቡነ እስጢፋኖስ በዛሬው ዕለት ፓትርያርኩ አቡነ ማቲያስ ‹‹አዲስ አበባ የእኔ ልዩ ሐገረ ስብከት በመሆኑና ማንም ሊያዝበት ስለማይችል ሊቀ ጳጳሱ በቦታቸው እንዲቀጥሉ በመወሰን የትናንቱን ውሳኔ ሽሪያለሁ››ማለታቸውን ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡
ስብሰባው ከሰዓት በኋላ ቀጣዩን አጀንዳ በማንሳት ከመወያየቱ በፊት ተቃውሞ እንዳላቸው የገለጹ ጳጳሳት ፓትርያርኩ የሲኖዶሱን ውሳኔ በመሻር ሊቀ ጳጳሱን በመንበራቸው እንዲቀጥሉ ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን በመግለጽ የቤቱን ውሳኔ እንዲያከብሩ ጠይቀዋል፡፡
ፓትርያርኩም በመጨረሻ የሲኖዶሱን ውሳኔ የመጨረሻ በማድርግ መውሰዳቸውን በመግለጽ አቡነ እስጢፋኖስ በሲኖዶሱ ውሳኔ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ሲኖዶሱ በነገ ውሎው በአቡነ እስጢፋኖስ ቦታ ሌላ ሊቀ ጳጳስ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ክልል መንግስት ተማሪዎችን ሰልፍ ከለከለ «ተማሪዎች ሰልፎች እንዳያደረጉ ለምን ተከለከሉ?» - ዓለምነው መኮንን

3 Comments

  1. WHY u distrub this man abune estifanos is that jealousy or again tribe issue ??????? lemen amhara honu new begid tigre weyem oromo becha mehone alebachew ? TIGRE ena oromowoch tewu agul zer mezerzer betam yedeberal

Comments are closed.

Share