November 24, 2017
3 mins read

ያልተጠናቀቁ የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ነዋሪዎችን አማረሩ

ayat condos

በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አለመጠናቀቃቸው ነዋሪዎችን ክፉኛ አማረረ፡፡ ቤቶቹ ግንባታቸው እና ሌሎች ጣጣዎቻቸው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ተብሎ በሚመለከተው አካል ተገልጾ ዕጣ ወጥቶባቸው ነበር፡፡ ዕጣው ከወጣ ረዘም ያለ ጊዜ ቢቆጠርም፣ ቤቶቹ ዕጣው ለወጣላቸው ነዋሪዎች ሊተላለፉ ግን አልቻሉም፡፡ ይህም የሆነው፣ ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ባለመጠናቀቃቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ መኖሪያ ቤቶቹ ወደፊትም መቼ ለነዋሪዎች እንደሚተላለፉ የታወቀ ነገር የለም፡፡

ስለ ጉዳዩ አስተያየታቸውን የሰጡ ወገኖች፣ ድርጊቱን ‹‹መንግስታዊ ውንብድና›› ሲሉ ገልጸውታል፡፡ መንግስት አልያም የአዲስ አበባ አስተዳደር ቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ፣ ቤቶቹ ገና ሙሉ በሙሉ ሳይጠናቀቁ ከነዋሪዎች ገንዘብ መቀበሉ መንግስታዊ ውንብድና መሆኑን እነዚሁ ወገኖች ይገልጻሉ፡፡ ድርጊቱ ገንዘብ ከፍሎ ቤት የሚጠባበቀውን ነዋሪ ያሳዘነ እና ያስቆጨ እንደሆኑም ከአስተያየት ሰጪዎቹ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ግንባታቸው ተጠናቋል ተብሎ በተለያዩ ሳይቶች ዕጣ የወጣባቸው የኮንዶሚኒዬም ቤቶች፣ ቀለም ያልተቀቡ፣ መብራት እና ውሃ የሌላቸው እንዲሁም ወደ መንደሩ የሚያስገባ በቂ የአስፓልት መንገድ ያልተሰራባቸው ቢሆኑም፣ መንግስት ግን ቤቶቹ ተጠናቀዋል ብሎ ገንዘብ በመቀበል ዕጣ አውጥቶባቸዋል፡፡ በተለይ በ2009 የመጨረሻ ወራት ላይ ዕጣ የወጣባቸው እና ክራውን ሳይት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ብዙዎችን እያማረሩ ይገኛሉ፡፡ ቤቶቹ የውሃም ሆነ የመብራት አገልግሎት ያልተገጠመላቸው ሆነው ተገኝተዋል፡፡
እንደዚሁም በሌሎች የአዲስ አበባ ክፍሎች የሚገኙ እና ተጠናቅቀዋል ተብሎ በመንግስት ልሳናት ፕሮፓጋንዳ የተረጨባቸው የኮንዶሚኒዬም ቤቶች፣ ገንዘብ ከፍለው በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎችን ክፉኛ አበሳጭተዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ወይ ከገንዘባችን ወይ ከቤታችን አልሆንንም ሲሉም እየደረሰባቸው ያለውን የገንዘብ እና የሞራል ኪሳራ ተናግረዋል፡፡ ቤቶቹ ከዚህ በኋላም መቼ ተጠናቅቀው ለነዋሪዎች እንደሚተላለፉ የታወቀ ነገር የለም፡፡ (BBN)

Previous Story

ፍትሐዊ ያልሆነ ግብር ተተመነብን ያሉ ነጋዴዎች እርምጃ ተወሰደባቸው

addis ababa city
Next Story

በኢትዮጵያ የድርቅ ተጎጂዎች ቁጥር መጨመሩ ታወቀ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop