November 24, 2017
3 mins read

ፍትሐዊ ያልሆነ ግብር ተተመነብን ያሉ ነጋዴዎች እርምጃ ተወሰደባቸው

ከነገዱት በላይ የሆነ ወይም ፍትሐዊ ያልሆነ ግብር ተተምኖብናል ያሉ ነጋዴዎች እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተገለጸ፡፡ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች፣ ፍትሐዊ ያልሆነ የግብር ተመን እንደተደረገባቸው የገለጹ ነጋዴዎች፣ ተቃውሟቸውን ሱቅ በመዝጋት እና አደባባይ በመውጣት ሲገልጹ እንደነበር ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን በበኩሉ፣ የነጋዴዎቹን ቅሬታ እንደሚፈታ ሲገልጽ ቢቆይም፣ በመጨረሻ ግን ተቃውሞ ሲያሰሙ በነበሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድባቸው ችሏል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ግብር እንደተተመነባቸው በመግለጽ ሱቅ እስከ መዝጋት የደረሰ የአድማ ተቃውሞ ሲተገብሩ የነበሩት የመርካቶ ነጋዴዎች የእርምጃው ግንባር ቀደም ሰለባ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከመርካቶ በተጨማሪም በፒያሳ አትክል ተራ፣ ሳሪስ፣ ኮልፌ እና በመሳሰሉት አካባቢዎች በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች የእርምጃው ሰለባ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ነጋዴዎቹ በገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን የተወሰደውን እርምጃ በመኮነን ተቃውሞ ቢያሰሙም ምንም ዓይነት መፍትኤ ሊያገኙ አለመቻላቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ በነጋዴዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ የገንዘብ እና የእስር ቅጣት ሲሆን፣ አብዛኞቹ ነጋዴዎች ግን በገንዘብ ቢቀጡም፣ የተወሰኑት ደግሞ በእስር ጭምር እንደሚቀጡ ታውቋል፡፡

ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ በተደረገ የቀን ገቢ ግምት ስሌት መሰረት፣ በነጋዴዎች ላይ የተተመነው ግብር ከፍተኛ እንነደበር በወቅቱ ሲገለጽ ነበር፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ነጋዴዎችም ምሬታቸውን በተላየዩ መንገዶች ሲገልጹ እንደነበርም አይዘነጋም፡፡ በወቅቱ የቀን ገቢ ተመኑ ሲሰራ፣ በነጋዴው ላይ ዋጋ እንደማይጨመር መንግስት አስታውቆ ነበር፡፡ ሆኖም ወደኋለ ላይ ግን ከፍተኛ የግብር ተመን ሲጣል ብዙዎችን አስደንግጦ ነበር፡፡ ከመደንገጣቸው የተነሳ በሽታ ላይ የወደቁ ሰዎች ስለመኖራቸው ታውቋል፡፡ መንግስት፣ የጀበና ቡና በምትሸጥ አንዲት ሴት ላይ፣ የ80 ሺህ ብር ግብር ተምኖ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ተመኑን ተከትሎ ንዴት የገባቸው ነጋዴዎ፣ ንግድ ፈቃድ እስከመመለስ ደረጃ ደርሰው ነበር፡፡ (BBN)

83133
Previous Story

የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ስብሰባ – አጫጭር መረጃዎች | ኣስገደ ገብረስላሴ (መቀለ)

ayat condos
Next Story

ያልተጠናቀቁ የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ነዋሪዎችን አማረሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop