October 20, 2017
1 min read

ሰሜን ሸዋ አማራውና ኦሮሞው በአንድነት ቆሞ ወያኔን እየተፋለመ ነው

ሙሉቀን ተስፋው

አገዛዙ በዴራ ሰሜን ሸዋ ዐማራና ኦሮሞን ለማጋጨት የሸረበው ሴራ ከሸፈ፤ የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

በሰሜን ሸዋ ዴራ ትናንት የዐማራና የኦሮሞ ተወላጆችን ለማጋጨት በአገዛዙ የተሸረበው ሴራ ሙሉ በሙሉ የከሸፈ ሲሆን በአገዛዙ ኃይሎች የሦስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ትናንት ጥቅምት 9 ቀን 2010 ዓ.ም ከጠዋት ጀምሮ በዴራና በመራህቤቴ የተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ተካሒደዋል፡፡

በተቃውሞው 7 ሰዎች በጥይት ተመትተው የሁለቱ ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ አንደኛው መራቤቴ ሆስፒታል ቢደርስም መትረፍ ባለመቻሉ የሟቾች ቁጥር ሦስት ደርሷል፡፡ ቀሪዎቹ 4ቱ ደግሞ በሪፈራል ወደ ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ተልከዋል፡፡
የአገዛዙ ኃይሎች ከቱቲ የመጡ ዐማሮች ኦሮሞዎችን ሊያጠፉ ነው ብለው ቢሰብኩም ‹‹ሁላችንም አንድ ነን›› በሚል ከመራህቤቴ፣ ብቸናና ዴራ የተሰባሰቡ ዐማሮችና ኦሮሞዎች ዛሬም ከአገዛዙ ኃይሎች ጋር ሲጋፈጡ መዋላቸውን ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የመራህቤቴ ከተማ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአጋዚ ወታደር እንደተከከበ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

2 Comments

  1. TPLF runs into the fire carrying a tons of kerosin. It will change into ash which remains on the paper in History.

  2. መርሐቤቴ – ላይቤት -ታችቤት የዶጋመድ አድርግ ይህንን የትግራይ ወራሪ ኃይል ክንድህን አሳየው ከአሮሞ ወንድሞጭህ ጋር
    እጅና ጉዓንት በመሆን !

Comments are closed.

Previous Story

ጥያቄ:- ወያኔ የተባለዉ አረም ከኢትዮጵያ ሳይነቀል የጣና አረም ተነቅሎ ጣና ሊድን ይችላል? የአማራ እና የኦሮሞ ወጣት የትብብር ማዕከል ምን መሆን አለበት?

addis ababa realethiopia 141
Next Story

በአዲስ አበባ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ800 በላይ ቤቶች በመንግስት ፈርሰዋል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop