October 20, 2017
1 min read

ሰሜን ሸዋ አማራውና ኦሮሞው በአንድነት ቆሞ ወያኔን እየተፋለመ ነው

ሙሉቀን ተስፋው

አገዛዙ በዴራ ሰሜን ሸዋ ዐማራና ኦሮሞን ለማጋጨት የሸረበው ሴራ ከሸፈ፤ የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

በሰሜን ሸዋ ዴራ ትናንት የዐማራና የኦሮሞ ተወላጆችን ለማጋጨት በአገዛዙ የተሸረበው ሴራ ሙሉ በሙሉ የከሸፈ ሲሆን በአገዛዙ ኃይሎች የሦስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ትናንት ጥቅምት 9 ቀን 2010 ዓ.ም ከጠዋት ጀምሮ በዴራና በመራህቤቴ የተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ተካሒደዋል፡፡

በተቃውሞው 7 ሰዎች በጥይት ተመትተው የሁለቱ ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ አንደኛው መራቤቴ ሆስፒታል ቢደርስም መትረፍ ባለመቻሉ የሟቾች ቁጥር ሦስት ደርሷል፡፡ ቀሪዎቹ 4ቱ ደግሞ በሪፈራል ወደ ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ተልከዋል፡፡
የአገዛዙ ኃይሎች ከቱቲ የመጡ ዐማሮች ኦሮሞዎችን ሊያጠፉ ነው ብለው ቢሰብኩም ‹‹ሁላችንም አንድ ነን›› በሚል ከመራህቤቴ፣ ብቸናና ዴራ የተሰባሰቡ ዐማሮችና ኦሮሞዎች ዛሬም ከአገዛዙ ኃይሎች ጋር ሲጋፈጡ መዋላቸውን ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የመራህቤቴ ከተማ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአጋዚ ወታደር እንደተከከበ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

2 Comments

  1. TPLF runs into the fire carrying a tons of kerosin. It will change into ash which remains on the paper in History.

  2. መርሐቤቴ – ላይቤት -ታችቤት የዶጋመድ አድርግ ይህንን የትግራይ ወራሪ ኃይል ክንድህን አሳየው ከአሮሞ ወንድሞጭህ ጋር
    እጅና ጉዓንት በመሆን !

Comments are closed.

Previous Story

ጥያቄ:- ወያኔ የተባለዉ አረም ከኢትዮጵያ ሳይነቀል የጣና አረም ተነቅሎ ጣና ሊድን ይችላል? የአማራ እና የኦሮሞ ወጣት የትብብር ማዕከል ምን መሆን አለበት?

addis ababa realethiopia 141
Next Story

በአዲስ አበባ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ800 በላይ ቤቶች በመንግስት ፈርሰዋል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop