በጎጃም ከሚያዝያ እስከ ነሐሴ ባሉት ወራት 8 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፤ ሰማያዊ ፓርቲ ማብራሪያ ጠየቀ

(ዘ-ሐበሻ) “በምስራቅ ጎጃም ስለተቃጠሉ ስምንት አብያተ ክርስቲያናት መንግስት ባስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሠጥ እንጠይቃለን” ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ። ፓርቲው ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው ላይ እንዳስታወቀው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በምስራቅ ጎጃም በአዋበልና አነደድ ወረዳ የሚገኙ 8 አብያተ ክርስቲያናት ከሚያዝና እስከ ነሐሴ 2005 ዓ.ም ባለው ጊዜ ብቻ ተቃጥለዋል።
መግለጫው የሚከተለው ነው፦

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

መንግስት በሚያስተዳድረው ሐገር ውስጥ የሚኖሩ ዜጎችን፣ ተቋማትን፣ የሀገር ሉዓላዊነትን፣ ታሪክን፣ ባህልን፣ የእምነት ነፃነትንና ደህንነትን ማስጠበቅ ተቀዳሚ ተግባሩ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በምስራቅ ጎጃም በአዋበልና አነደድ ወረዳ የሚገኙ ስምንት አብያተ ክርስትያናት ከሚያዚያ እስከ ነሐሴ 2005 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ብቻ በእሳት ተቃጥለው በቤተክርስቲያናቱ ውስጥ የሚገኙ ነዋየ ቅድሳት፣ ልዩ ልዩ አልባሳት፣ ብዙ መጽሐፍትና ንብረት ወድሟል፡፡
እጅግ የሚያሣዝነው የአካባቢው ነዋሪዎች በመንግስት በኩል ምክንያቱ ታውቆ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሠድ በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ሰሚ ጆሮ አላገኙም፡፡ ጉዳዩንም የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቀው በክልሉ ቴሌቪዥን በዜና መልክ እንዲገለፅ ያደረጉት ጥረት አልተሳካም፡፡ በአንድ አካባቢ በተለያየ ጊዜ በተደጋጋሚ በቤተክርስትያን ላይ የማውደም ተግባር ስምንት ጊዜ ሲፈፀም በሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን አንድም ቀን አለመገለፁና በመንግስት በኩል መፍትሔ አለመስጠቱ ፓርቲያችንን ከልብ አሳስቦታል፡፡ በመሆኑም እነዚህ ከታች የተዘረዘሩት አብያተ ክርስቲያናት፡-
1. አንጋጫ ኪ/ምህረት 2. ዳገት ሚካኤል 3. የደርበን ሚካኤል
4. ዋሻ መድሀኒዓለም 5. መንክር ማሪያም 6. ቀዝቀዝ ገብርኤል
7. ደማም እየሱስ 8. ምስለ ዋሻ ጊዮርጊስ
አንዳንዶቹ ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ የወደሙ ሲሆን የተወሰኑት በአካባቢው ሕብረተሰብ ጥረት በከፊል ተቃጥለው የተወሰነ ንብረት ሊተርፍ ችሏል፡፡ ፓርቲያችን በህግ ተመዝግቦ ህጋዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ተወዳደሮ የመንግስት ሥልጣን ከመያዝ በተጨማሪ በተለያየ ጊዜ በሐገርና በህዝብ ላይ የሚደርሱ ችግሮችን መከታተልና በሚመለከተው አካል መፍትሄ እንዲያገኙ ጥረት ማደረግ ስለሆነ በመንግስት በኩል ጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶት የቃጠሎው ምክንያት ተጣርቶ ድርጊቱን የፈፀመው አካል በህግ ተጠያቂ እንዲሆንና ይህም ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲገለፅ እያሳሰብን እንዲህ ዓይነቱ በሕዝብ አመኔታ የሚጣልባቸው ተቋማትን የማውደም ተግባር ወደፊትም እንዳይደገም በመንግስት በኩል አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
መስከረም 26 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ተጨማሪ ያንብቡ:  Meles Zenawi’s VOA blacklist unveiled

5 Comments

  1. yet neberachu esikezare bemn miknyat enidemkatlim libonachu bednib tawkutalachu hitsanat aregawiyan enatochi sitaredu semitachu enidalsema ayitachu enidalaye ewinet tekorkurachu newni?

  2. ye tigre gujele cadrewoch nachew yihen dirget yemefesimut-mikinyatum ye ethiopia tarik meseret ke aksum sayihone ke Amhara kilil endememeneche bedenib tenkikew yakutal-enam betechalachew meten yihin huneta lemefaq yemyadergut ekuy sera endehone melaw ye Amhara hizib legenezebew yasfeligal-awo ke aksum befit ye tana gedamat, ye misirak gojjam mertolemaryam gedamat, ye debub wollo tedbab maryam(tedbab Tsion), atrnose Maryam, deber kelanch, geiyorgis ze gasicha…tekedami asharawoch endehonu letaweq yigebal-ye tigre gujele mengist yadergew zerefa alibeqa bilot chirashinu leyatefa yemefelig tarik aliba ye saba deqaloch nachew!

  3. thumbs up! for those who did this burn more,support burning by giving kerosene orthodox church and amhara are a two sides of acoin no relation between chrstianity and ethiopian orthodox church it is just amhara made religion bury amharas by burning their soul.

  4. Well; ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH NO ONE WILL NOT BURN IT DOWN. EOTC IS AN IMOVABLE ROCK. U JUST DESTROY THE MATERIAL NOT EOTC. IT IS OKAY. I REJOICE . GO HEAD BURN IT DOWN . GOD IS IN CONTROL. DISPARATE DEMON IS TOO SICK. WE KNOW EVERY SOURCE WHAT DEMON IS TRY TO SAY. BUT DEMON U R TOO LATE AND TOO SIMPLE MIND. CORRUPT DEMON DIRTY DEMON BLIND AND DEAF DEMON. IGNORANT DEMON MATERIALIST DEMON, DEMON THE god OF THIS WORLD we know in the last days he destroy the true faith. Destroying church is not the End of EOTC. IT IS ALL ABOUT DEMON. DEMONS PROPAGANDA. @ JADPIK, WELL, EOTC EGYPT, ROMANIA , AND PART OF INDIAN COPTIC ORTHODOX THAT IS TRUE THEY ARE NOT THE SAME WITH THOSE LIAR AND LOSER CHRISTIANS. BECAUSE OF GEO, POLITICAL, AND SUPERIORITY REASON THEY DESTROY MORE THAN 100000 WORDS FROM THE HOLY BIBLE TO FIT THEIR CORRUPTED DOCTRINE. TRUTH IS TRUTH EVEN IF EVERYONE DENIES IT. MONEY, POPULARITY,AND MILITARY POWER THEY CAN SPEAK THEY CAN DO WHAT EVER THEY WANT. BUT WHOSE AGENDA IS THIS? Who is behind this dirty game? Very simple. It is easy to read the simple mind Demon. Funny christianity funny theology universities, collages and etc. Nobody, NOBODY, NOBODY can buy it sell it or own the power of God. Ur popularity, money and excessive power didn’t work. Read the holy book baby OUR ROTC NOT FOUNDED BY FOOD, DEAD PERSON CLOTH, GIVE AWAY STUFFS, OR TO FLY TO RICH COUNTRIES. BUT I TELL I TELL U EVEN NOT BY ANYBODY WISHES. BUT IT IS BY ALMIGHTY GOD READ ACT 8:26 – …… JOB 8:8-11 ……..EOTC STILL EOTC NO ONE NO ONE NO ONE WILL NOT DESTROY ROTC MAYBE MATERIALS . WE WILL GET TOGETHER ON THE OPEN FIELD MATERIALS ARE NOT EOTC PROBLEM. DEMON IS MATERIALIST.

Comments are closed.

Share