September 21, 2017
3 mins read

ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ የተላከ ስኳር ድንበር ላይ እየተበላሸ እንደሚገኝ ተጠቆመ

bbn daily ethiopian news march 2

የህወሓት መንግስት ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ ያጓጓዘው ስኳር ድንበር ላይ ለብልሽት እየተዳረገ መሆኑን መረጃዎች አመለከቱ፡፡ በሀገር ውስጥ በቂ የስኳር ምርት ሳይኖር ለኬንያ ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር የሸጠው የህወሓቱ መንግስት፣ ስኳሩን ወደ ኬንያ ቢያጓጉዝም ድንበር ላይ ታግቶ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህም የተነሳ ከ110 በላይ ስኳር ከኢትዮጵያ ጭነው ወደ ኬንያ የተጓጓዙ ተሳቢ መኪኖች ከወር በላይ ሞያሌ ድንበር ላይ ለመቆም ተገድደዋል፡፡

ችግሩ በምን ምክንያት እንደተፈጠረ ለጊዜው የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ከ110 በላይ ስኳር የጫኑ መኪኖች ድንበር ላይ መቆማቸውን ተከትሎ ስሞታ ማሰማት ጀምረዋል፡፡ ስኳሩን ወደ ኬንያ እንዲያጓጉዙ የተመረጠው የመኪኖቹ ባለንብረት ድርጅት ስሞታ ማቅረብ የጀመረው ከወር በፊት ነበር፡፡ ከዚህ ቀደም ሞያሌ ድንበር ላይ እንዲቆሙ መገደዳቸውን ተከትሎ ለመንግስት ስሞታ ያቀረበው የመኪኖቹ ባለቤት ድርጅት፣ ከኬንያ መንግስት ጋር በተደረገ ስምምነት መኪኖቹ ወደ ኬንያ እንዲገቡ እንደተፈቀደላቸው ተነግሮ ነበር፡፡ ሆኖም ስኳር የጫኑት መኪኖች እስካሁን ድረስ ወደ ኬንያ መግባት አልቻሉም፡፡ በዚህም የተነሳ ስኳሩን የሚረከባቸው አካል አጥተው ከወር በላይ ስኳሩን እንደጫኑ ለመቆም ተገድደዋል፡፡

አንድ ኪሎ ስኳር እስከ 60 ብር ድረስ ከሚሸጥባት አትዮጵያ ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር ወደ ኬንያ መጓጓዙ ብዙ ሲያነጋግር ነበር፡፡ ስኳር ለኬንያ በተሸጠ በ15 ቀናት ውስጥ በሀገር ውስጥ የስኳር ገበያ ላይ ከፍተኛ መናጋት የተፈጠረ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስም በኢትዮጵያ በቂ የስኳር አቅርቦት አለመኖሩን ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡ በኢትዮጵያ በቂ የስኳር አቅርቦት አለመኖሩን ተከትሎም አንድ ቤተሰብ መንግስት በሚመድብለት ኮታ ወይም መጠን መሰረት ስኳር ለመግዛት ተገድዷል፡፡ የህወሓት መንግስት ለኬንያ የሸጠው ስኳር መጠን 2 ነጥብ 2 ሚሊዬን ዶላር የሚያወጣ ነው፡፡

chilga
Previous Story

ሰይጣንን ተንኮል ያስተማረው ወያኔ እያለ የአማራ ህዝብ እረፍት እንዳያገኝ የማይቆም ትግል ውስጥ ገብቷል

my
Next Story

ከማይናማር ለተፈናቀሉ ሙስሊሞች እርዳታ ሲያጓጉዝ የነበረ መኪና ተገልብጦ ሰዎች ሞቱ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop