በዛሬው እለት ወገራ ላይ ውጊያ አለ

ከሙሉነህ ዮሐንስ

(ሰኔ 22 2009)  ትናንት በላክነው ማስጠንቀቂያ ወያኔ ወደ ሰሜን ጎንደር የተለያዩ ቦታወች ሰራዊት እየላከ ስለመሆኑ ገልፀን ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበን ነበር። ሰላማዊ ህዝቡን ማሸበር የያዘው ወያኔ የገበሬውን መሳሪያ ነጠቃ ሙከራ ያደርጋል። በዚህ የተበሳጩት ገበሬወች የወያኔን አገልጋይ ሰራዊት ገጥመዋል። ከገበሬወቹ መካከል ዋስትና እንሰጣቹሃለን ምህረት ግቡና በሰላም ኑሩ ብለው ለመሸምገል የሞከሯቸውን ሁሉ የጥቃቱ ኢላማ አድርገው ነበር።

ይህን ጥቃት የመከቱት ገበሬወች ወደ በርሃ ወርደዋል። አስደንጋጭ ምት የደረሰበት የወያኔ ሰራዊት እየተተራመሰ ሲሆን አሁንም ቢሆን ህዝቡ እራሱን በንቃት መጠበቅ አለበት። የግጥሚያውን ልዩ ቦታና የጎበዝ አለቆቹን ስም ከመጥቀስ ተቆጥበናል። በዚህ ግንባር ከተሳተፉት የጎበዝ አለቆች መካከል ባለፈው አመት አምባጊዮርጊስ ላይ ወያኔ በህዝቡ ላይ የፈፀመውን የጅምላ ጭፍጨፋ አፀፋ በመመለስ እጅግ ስመጥር የሆነ ጀግና ይገኝበታል።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ ትናንት የሚከተለው መልዕክት ተላልፎ ነበር::

 

በሰሜን ጎንደር አንባ ጊወርጊስ አካባቢ፣ ወደ ቆላ ወገራ እና እንቃሽ ውስጥ ድረስ ለሚንቀሳቀሱ የጎበዝ አለቆች ሙሉ መረጃ ለመሰብሰብ እና የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ያስችለኛል በማለት ወያኔ በከፍተኛ ሁኔታ አስቦና ወጥኖ ይበጀኛል ያለውን ዘዴ እየሞከረ ነው።

አካባቢውን ጠንቅቀው ከሚያውቁት እና ታማኝ ናቸው ተብለው በተመረጡ ወታደሮቹ ልክ አርሶ አደር በመምሰል የኮንትሮባንድ ጥይት ሻጭ በማስመሰል ረከስ ባለ ዋጋ እየሸጡ በድብቅ በያዙት ዘመናዊ የኤሌክትሮኒስ መሳርያዎች በመታገዝ ስለላውን ለማድረግ ተልእኮ ተሰጥቷቸው መሰማራታቸው ተደርሶበታል። ትንሽ ቁጥር ያላቸውን ባንዳዎች ሙሉ ለሙሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ በሚላበሱ ዘዴ በጭነት በአይሱዚ መኪና ልኳል፡፡ እናም ይህ መልእክት ቶሎ ይተላለፍ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት በጌዴኦ ዞን የተፈናቀሉ ሰዎችን መልሶ ለማቋቋም ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ የፕሮጀክት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

 

4 Comments

  1. ሙሉነህ ዮሐንስ
    One can appreciate your reports. But its reliability needs thorough investigation.You are telling readers that peasants (any one anti-TPLF forces) are fighting with TPLF. Yet you don’t tell don’t tell where the fighting took place. Whom do you hide because the enemy Tigre is involved in the fighting, according to you. This is many fraud reports I am reading. Is this a continuation of fabricated lies of habesha?

  2. ሙሉነህ ዮሐንስ, you are doing the right thing. No, the location of the fighting should not be disclosed. Disclosing the location will tell Woyanie, which might not know necessarily, where to send additional forces.

  3. Please give due credit to Amara resistnace fighters. Ginbot 7 does not have army throughout Amara region, if at all it has any. If G7 is and Amara resistance forces are working together, then we should report “Ginbot 7 and Amara Resistance Army”.

Comments are closed.

Share