ወያኔ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ማጋጨቱን ተያይዞታል

የወያኔው መሪ ደብረጽዮን በአዲስ በቃኘው ዘረኛ ፖለቲካ መሰረት በሕዝብ መሃል የእርስ በርስ ጭቶችን ማስፋፋት በሚል በሞያሌ ገሬ(ሶማሌ) ና ቦረናዎችን፤ ሀመርን ከኤርቦሬ፤ ቦዴይን ከኮንሶ …ወዘተ ማጋጨቱ በሰፊው ተከስቷል በሚል ወያኔ ላይ ክስ ቀርቧል። በሶማሌዎችና በኦሮሞዎች መሀል ተጭሮ የነበረው ግጭትም የበረደ ቢመስልም ወያኔ ጸረ ኦሮሞ ሴራውን አጠናክሮ መቀጠሉም ተጋልጧል።

የሕዝብን አንድነት ማፍረስ ለወያኔ ህልውና ወሳኝ በመሆኑ ጽንፈኞችን በየአቅጣጫው አሰማርቶ በተለይም አማራና ኦሮሞውን ለማጋጨት በስፋት እየጣረ ያለው ወያኔ አስመሳይ ቡድኖችንም ማቋቋሙም ተጋልጧል።

ምንጭ ፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ

ተጨማሪ ያንብቡ:  አዲሱ የእስር ዘመቻ | ቆይታ ከጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ጋር
Share