የሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሰልፍ በእምቢተኛው ፌደራል ፖሊስ ታገተ

(ዘ-ሐበሻ) “ሰላማዊ ትግል ፈተናው ከባድ ነው። እንደዚህ ቢፈታተኑንም እኛ ተስፋ አንቆርጥም። ይህ የትግላችን መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም። እየወደቅንም እየተነሳንም ቢሆን ትግሉን ከዳር እናደርሳለን።” ነበር ያለችን ወ/ሪት መሠረት የዛሬው የሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በፌደራል ፖሊስ ከታገተ በኋላ። “መንግስት ሰልፉን ለምን በመስቀል አደባባይ እንዳይደረግ እንደፈራ ይገባናል። በጃንሜዳ አድርጉ የሚል የሰልፍ ፍቃድ የሰጠን ጃንሜዳ የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ እንጂ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጊያ ቦታ አለመሆኑን እያወቀ ጃንሜዳ በግቢ የታጠረ ስለሆነ መንግስት ድምጽን ለማፈን እና ተቃውሞውን ለመቆጣጠር በማሰብ ይህን ቢያደርግም እኛ ድምጻችንን መንግስት ብቻ ሳይሆን የነፃ ሚዲያ ዘገባ የማያገኘው ሕዝባችን እንዲሰማ በማሰብ ጭምር ሰልፉን መስቀል አደባባይ ለማድረግ ቆርጠን ነበር። ሕገመንግስቱን ለማስከበር የቆሙት ፌደራል ፖሊሶች የኢሕአዴግን ሥርዓት ስለሚያስከበሩ ሰልፋችንን ቢያግቱትም ሰላማዊ ተቃውሟችን ግን አሁንም እንዳስበረገጋቸው ተረድተናል፡” ብላለች ወ/ሪት መሠረት።

በደማቅ ሁኔታ የተጀጀመረው የሰማያዊ ፓርቲ የዛሬው የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በፌደራል ፖሊሶች እገታ ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይሻገር ቢታገድም ለተቃውሞ የወጣው ሕዝብ ግን ድምጹን ሳያሰማ አልቀረም። መቶ ሜትር ሳይሻገር በመንግስት ኃይሎች የታገተው ይኸው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የፌደራል ፖሊሶች ሕዝቡን ካሜራ እንዳያነሳ ከመከልከል በተጨማሪ ቪድዮና ፎቶ ግራፍ የቀዱ ሰዎችን ካሜራውን እየተቀበሉ ፎቶ ግራፉን ማስጠፋታቸውን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ ዘገበዋል። ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ከፌደራል ፖሊስ ያመለጡ ፎቶ ግራፎች ፌስቡክን በመሳሰሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተለቀዋል።

ተቃዋሚው ሰልፈኛ በ እስር ቤት ያሉ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች እንዲፈቱ የጠየቁ ሲሆን
“ፍትህን መጠየቅ አሽባሪነት አይደለም!
ነፃነት እንፈልጋለን!
እኛ አሽባሪ አይደልንም!
ፍትሕ እንፈልጋለን!
የሙሰሊም ኮሚቴ ይፈቱ!
ዜጎችን ማፈናቀል አግባብ አይደለም!
አንለያይም!
አንለያይም!
ፍትህን ያሉ ቃልቲ ገቡ!
ፍትህ ናፈቀኝ!
የሚሉና ሌሎችንም መፈክሮችን ሲያሰሙ ተደምጠዋል። ለተቃውሞ የወጣው ህዝብ በፌድራል ፖሊሶች ተከልክሎ ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይሄድ ቢታገትም ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በመመልሰ እንዲሁም በአራት ኪሎ አደባባይ ላይ ድምጹን በማሰማት የሰላማዊው ተቃውሞ ሰልፍ በሰላም ተጠናቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰበር ዜና፡ ጳጳሳት የፓትርያርክ ምርጫው ወደ ግንቦት እንዲዛወር ጥያቄ አቀረቡ

“ሰላማዊ ትግል የሚጠይቀውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነን” ያለችው ወ/ሪት መሠረት “ትግሉ ተጀመረ እንጂ አላለቀም፤ በመንግስት ወከባ የሚደነግጥ የለም” ስትል ለዘ-ሐበሻ የሰጠችውን አስተያየት አጠናቃለች።

የፊታችን እሁድም እንዲሁ አንድነት ፓርቲ እና 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ በመስቀል አደባባይ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ይታወሳል።

5 Comments

  1. ሰላማዊ ሰልፍና ሰላማዊ የፓርላማ እስጥ አገባ ድራማ ካበቃ ዘመናት ተቆጥረው 23 ዓመታት አለፉ። የጦርነት ትግል የማይቀር ጉዳይ መሆኑን ባርነት የሰለቸውና ያንገሸገሸው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያውቃል። የፋሽስት ወያኔ ዱላ እራሱን እንዲደበድብ ለማድረግ ቆራጥነት ካሁኑ ነው። ስለፋሽስት ወያኔ የማያውቅ ኢትዮጵያዊ የለም።

  2. why only the BLUE party all ETHIOPIANS that they think this devil weyne got to be out sight have to participate in the protest next time when the 33 different parties go out to protest all the rest of us ETHIOPIANS join them let weyanes shit in their pants let us be all together so that we can overcome this ugly obstacle.
    DEATH TO weyanes…………………let ETHIOPIA FIRST.

  3. The weyane creation semayawe party is joking .semayawe party is a fake opposition created by berket Simon to sebtitue edepa party.the so called enginer yelkal and lidetu are the personality created by weyane for the next fake election.

  4. tagaye le tegel bota aye meretem…ye gede selefu Meskel Adebabaye mehon yelebetem…
    blue party…tagaye ke honu…jalemeda ayedelem…sendafa be honem mehed newu..bota eyemeretu tegel yelem…
    hegen ye mayakeber party…hege men endehon lenegerewu yegebal….
    blue party…jebedejenet eyabezu newu..hezebem le hege ke mayegeza party gara tekelakelo..ayeselefem….
    ke ethiopia tekawami party yelek ye ethiopia hezeb..ye belet neku newu.
    …le hege ye mayegeza party berasu geze yetefal…

Comments are closed.

Share