March 28, 2017
2 mins read

በአንድ ቀን በአዲስ አበባ፣ በወልቃይትና ባህርዳር የሕወሓትና ብአዴን ንብረቶች ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ

ከሙሉነህ ዮሐንስ

ቃጠሎ አንድ
አዲስ አበባ

ልዩ ስሙ ጃክሮስ በሚባል አካባቢ አ.አ ውስጥ በሚገኘው እጅግ ግዙፍ በሆነው የወያኔ ኤፈርት ሁሉን አቀፍ አስመጪና መላኪያ መጋዘን እና ፋብሪካ ክፍል በተቀነባበረ ሴራ በተለኮሰ እሳት በትንሹ እስከ 40 ሚሊዎን ብር የሚገመት ንብረት ወደመ፡፡ በርካቶችን ለእስራት እየዳረገ ነው፡፡

ቃጠሎ ሁለት
ወልቃይት

440 ኩንታል ጥጥ ወልቃይት ላይ ተቃጠለ። ጥቃቱ የወያኔን የንግድ ጥቅሞች ላይ ጉዳት ለማድረስ ነው የሚሉ ዘገባዎች ወጥተዋል።

ቃጠሎ ሶስት
ባህር ዳር

አመልድ (እየተጣራ ነው) እየተቃጠለ ነው የሚል መረጃ አሁን መጣ። ይህም የወያኔ/ብአዴን ተቋም መሆኑ ነው።
እናም በወያኔ ላይ አዲስና የተቀነባበረ ጥቃት እየተፈፀመ ከሆነ መቆሚያ አይኖረውም። ምክንያቱም ጥቃቱን ለማድረስ መስዋእትነት አያስከፍልም:: ጉዳቱ ግን ከፍተኛ ነው። ወያኔ ደግሞ ገንዘብ በጣም ታፈቅራለች…ይህ ያንኮታኩታቸዋል…ወየው ለማረት ወየው ለኤፈርት…

በሌላ በኩል በባህርዳር የተከሰተውን ቃጠሎ ተከስቶ ከፍተኛ ተኩስ ማምሻውን እየተሰማ መሆኑን ከስፍራው የመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ::

ዝርዝር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን

1 Comment

  1. ግንቦት0 እኔነኝ ያደረኩት ለማለት እየተቁነጠነጠ ነዉ። ዘዴውን ኮለኔል ፍፁምን መላበለን እያሉ ነው። ምናልባትም ጋድ ኮለኔል ፍፁም በአዳዲስ የግንቦት0(tpdm)ፎቶዎች ብቅ ሌል ይችላል።

Comments are closed.

32165
Previous Story

በመደብ ትግል የሚያምኑ በመደብ ትግል ይደመሰሳሉ – ሸንቁጥ አየለ

Next Story

ይበቃል ከአንግድህ …….የበላይ  ለመሆን

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop