March 28, 2017
2 mins read

በአንድ ቀን በአዲስ አበባ፣ በወልቃይትና ባህርዳር የሕወሓትና ብአዴን ንብረቶች ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ

ከሙሉነህ ዮሐንስ

ቃጠሎ አንድ
አዲስ አበባ

ልዩ ስሙ ጃክሮስ በሚባል አካባቢ አ.አ ውስጥ በሚገኘው እጅግ ግዙፍ በሆነው የወያኔ ኤፈርት ሁሉን አቀፍ አስመጪና መላኪያ መጋዘን እና ፋብሪካ ክፍል በተቀነባበረ ሴራ በተለኮሰ እሳት በትንሹ እስከ 40 ሚሊዎን ብር የሚገመት ንብረት ወደመ፡፡ በርካቶችን ለእስራት እየዳረገ ነው፡፡

ቃጠሎ ሁለት
ወልቃይት

440 ኩንታል ጥጥ ወልቃይት ላይ ተቃጠለ። ጥቃቱ የወያኔን የንግድ ጥቅሞች ላይ ጉዳት ለማድረስ ነው የሚሉ ዘገባዎች ወጥተዋል።

ቃጠሎ ሶስት
ባህር ዳር

አመልድ (እየተጣራ ነው) እየተቃጠለ ነው የሚል መረጃ አሁን መጣ። ይህም የወያኔ/ብአዴን ተቋም መሆኑ ነው።
እናም በወያኔ ላይ አዲስና የተቀነባበረ ጥቃት እየተፈፀመ ከሆነ መቆሚያ አይኖረውም። ምክንያቱም ጥቃቱን ለማድረስ መስዋእትነት አያስከፍልም:: ጉዳቱ ግን ከፍተኛ ነው። ወያኔ ደግሞ ገንዘብ በጣም ታፈቅራለች…ይህ ያንኮታኩታቸዋል…ወየው ለማረት ወየው ለኤፈርት…

በሌላ በኩል በባህርዳር የተከሰተውን ቃጠሎ ተከስቶ ከፍተኛ ተኩስ ማምሻውን እየተሰማ መሆኑን ከስፍራው የመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ::

ዝርዝር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን

1 Comment

  1. ግንቦት0 እኔነኝ ያደረኩት ለማለት እየተቁነጠነጠ ነዉ። ዘዴውን ኮለኔል ፍፁምን መላበለን እያሉ ነው። ምናልባትም ጋድ ኮለኔል ፍፁም በአዳዲስ የግንቦት0(tpdm)ፎቶዎች ብቅ ሌል ይችላል።

Comments are closed.

32165
Previous Story

በመደብ ትግል የሚያምኑ በመደብ ትግል ይደመሰሳሉ – ሸንቁጥ አየለ

Next Story

ይበቃል ከአንግድህ …….የበላይ  ለመሆን

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop