September 11, 2013
2 mins read

ርዕዮት ዓለሙ በ እስር ቤት የረሃብ አድማ ጀመረች፤ በሙስና የታሰሩት ኮ/ል ሃይማኖት እያስፈራሯት መሆኑን ተናገረች

ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ
ርዕዮት ዓለሙ በ እስር ቤት የረሃብ አድማ ጀመረች፤ በሙስና የታሰሩት ኮ/ል ሃይማኖት እያስፈራሯት መሆኑን ተናገረች 1
የ2005 ዓ.ም በዘ-ሐበሻ አንባቢዎች የዓማቱ ምርጥ የሴት ጋዜጠኛ በሚል የተመረጠችውና በእስር ቤት እየማቀቀች የምትገኘው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ከትላንት ጀምሮ ከእናት ከአባት እና ከነፍስ አባት ውጪ እንዳትጠየቅ በመከልከሏ የረሃብ አድማ ላይ መሆኑና ጋዜጠኛ በፍቃዱ ኃይሉ በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው መረጃ ገለጸ።

በቅርቡ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ ከተመሰረተባቸው ውስጥ አንዷ የሆኑት ኮ/ል ሃይማኖት (በተመሳሳይ ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው እና የጉምሩክ አመራር የነበሩት አቶ ገ/ዋህድ ባለቤት)፤ ርዕዮት ያለችበት ክፍል እንዳሉና፤ ከኮ/ል ሃይማኖት በተደጋጋሚ ዛቻ ፣ ስድብ እና ማስፈራሪያ እየደረሰባት እንደሆነ በዛሬው እለት ሊጠይቋት ለተፈቀደላቸው ለእናቷ ገልፃለች፡፡ እንዲሁም ከማረሚያ ቤቱ የሴት ፖሊሶችና እና ደህንነቶችም ተመሳሳይ ማስፈራሪያ፣ ስድብ እና ዛቻ እየበረታባት እንደሆነ ተናግራለች፡፡

ዛሬ ለበዓል ሊጠይቋት ከሄዱ ቤተሰቦቿ እና ጓደኞቿ መሃል እናቷ ብቻ እንዲያዩአት የተፈቀደላቸው ሲሆን፤ እየደረሰባት ያለውን የሰብአዊ ጥሰትም በመቃወም ከትላንት ጀምሮ የምግብ አድማ ላይ መሆኗን በመግለጿ፤ ይዘውላት የሄዱትን ምግብ መልሰውታል ያለው ጋዜጠኛው “በዚህ ስሜት ውስጥ ያሉትን የርዕዮት ቤተሰቦች ለማፅናናትም የሚከብድ ነገር ነው፡፡” ሲል ስሜቱን ገልጿል።

2 Comments

  1. REYOTYEE !!!!!!!!!! please!!! please!!!!!!! don’t go further with hunger strike,it won’t help you a bit, except making these cruel savage idiots happy that is what they want to kill your self that is their mission so don’t be trapped in this situation what you have to do is pretend that you are happy even though you aren’t always think there is always another time or the right time for you too.
    hope this new year is the one which drive these skanks out of our country once for all .

Comments are closed.

የመውጫ ቪዛ 022 1 1 1
Previous Story

የማለዳ ወግ …አምላክ ሆይ ! የአዲሱ አመት ተስፋና ምኞታችን አሳካው !

Andualem Arage kids
Next Story

የዓመቱ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ምርጥ ሰው – የአንዷለም አራጌ የሕይወት ገድል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop