September 8, 2015
22 mins read

የአርበኛው ኑዛዜ፣ ከፍል 1 ለቅምሻ – መልኬ መንግስቴ

melekie

ይህን ለሚመለከተው ሁሉ የአክብሮት ሰላመታየን አቀርባለሁ|

ለረጅም ጊዜ ማስታወሻ ስይዝ ቆይቸ የደረስኩት መጽሀፍ ወደማጠናቀቅ ስለደረሰኩ አምላክ ፈቃዱ ከሆነ በቅርብ ጊዜ ለሕዝብ ለማበርከት በዝግጅት ላይ ነኝ፣ይህን ለቅምሻ የአቀረብኩት እንደመንደርደሪያ ሁኖ ዝርዝር ሁኔታውን በመጽሐፋ ውስጥ ሰለተጠቃለለ መጽሀፋን እንዲመለከቱልን በአክብሮት እጋብዛለሁ፣ ስደት.ወደ ሱዳን፤
በደርግ ዘመነ መንግሰት በነበረው ስርዓት ተጠቃሚ አልነበርኩም እንደሌላው ኢትዮጵያዊ በደሉ እኔንም ደቁሶኝ አልፎአል፣በዚያ ዘመን በፀረ መንግስት ተከስሼ ታስሬ ነበር  በእስር ሁነው የመሞቻቸውን ጊዜ ከሚጠባበቁት ሙታን አንዱ ነበርኩ፣በራሴ ላይ ወስኝ በዓምላክ ፈቃድ ከእስር አምልጨ ወደበርሀ ገባሁ‹ ከወህኔ ለማምለጥ የነበረው ፈተና ከሞት ጋር የሚደረግ ትንቅንቅ ስለነበር ከስር ከአመለጥኩ በኋላ በዘመኑ የነበሩት የአካባቢ ምልሻወች አመለጠ ያዙት ወይም ግደሉት ሹመት ይጠብቃችሁአል የሚለው ትእዛዝ በሹመት ፈላጊና ከሞት ለማምለጥ የነበረው ፍጥጫና ግብ ግብ በመላ ከባድ ፈተና ነበር/ከእስር አምልጨ በርሀ ከሚታገሉ አማጽያን ጋር ተቀላቀልኩ ከተወሰነ ውጣ ውረድ በኋላ ሱዳን በስደት ቆየሁ በምህረት ወደአገሬ ተመለሼ ዛሬ በስልጣን ያለው መንግሰት እስከመጣ ድረስ ከአገሬ በሰላም እኖር ነበር፤

የደብረታቦር መያዝ ድጋሜ ከአሰርቤት ማምለጥ ስደት ወደኬንያ፣

የህዋት አማጽያን የትግራይን ምድር በመላ ከተቆጣተሩ በኋላ ቀጥለው የተቆጣጠሩት ደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ነው እኔ ደብረታቦር ከተማን ሲቆጣጠሩ ከቤቴ ነበርኩ  ለውጥ እንዲመጣ የደርግን መንግስት ከተቃወሙት አንዱ ዜጋ ነበርኩ ማለት እችላለሁ.የደርግ መንግስት ወድቆ እታሰራለሁ እሰደዳለሁ የሚል ግምት አልነበረኝም ያሰብኩት ሣይሆን ቀርቶ ያልጠበኩት ተከሰተ፣የስደትን መከራንና ውጣ ውረድ ስለማውቀው ድጋሜ ከስደት ላይ ላለመውደቅ ቤተሰቦቸንም ከችግር ላይ ላለመጣል ሁሉንም ነገር ዓሜን ብየ ተቀብየው ነበር በሰላም ለመኖር ያላደረኩት ጥረትና ሙከራ አልነበረም፣የሀገርንና የወገንን በደል ማየትና መሼክም አልቀበልም በማለት ሲያስቸግረኝ የኖረው ህሊናየ ክብደቱና ጫናው ስለበዛብኝ ወደኬንያ ለስደት በቃሁ፣ቤቴና ንበረቴ በመላ ተወረሰ ወንድሞቸ አለቁ/ኬንያ አዲስ ትግል ለመጀመር ከደቡብ ኢትዮጵያ የተሰደደው ወታደር ከብላቴን ማሰልጠኛ የተሰደደው የዮንበርስቲ ተማሪዎች ጭምር እጅግ በርካታ ሠራዊት ነበር የደርግ ባለስልጣኖች ነበሩ ለትግል ማሰባሰብ ቀርቶ እነሱም ሼሸጉኝ ብለዋል፣አንድ የሲብል ባለስልጣን ስማቸውን ከመጥቀስ ተቆጥቤ ወደዝንባቦይ ህደው ፐሬዘዳንቱን አነጋግሬ መጣሁ ከኢትዮጵያ ምድር ገብታችሁ ከአንድ ቦታ ሁናችሁ ጥሩኝ መጥቸ ከናተ ጋር እዋጋሁ ብለዋል የሚለው የትግል ጥሪ ብቅ ስላለ ብዙ ሰወችን ማሰባሰብ ተሞክሮ  ነበር በዚህ ሄደት ላይ እንዳለ ድምጥ በለለው መሳሪያ ብዙ ሰወች መገደላቸው ነገሩን ውስብስብ እያደረገው መጣ፤ለመደራጀት የተመረጠው ቦታ ካኩማ የስደተኛ ካነፐ ነበር ይህ ስፍራ ለኢትዮጵያ ደንበር ቅርብ ነበር፣ጋንቤላጉዞ፣በቁጥር ለመጀመሪያ ጊዜ 75 ወታደሮች ተዘጋጅተው በጎምጎፋ አቋርጠው ጋንቤላ ገቡ ኮሎኔል ጋራንግ በፊት ፈቅደው ነበር በኋላ ግን በ24 ስዓት ካልወጣችሁ እርምጃ ውሰዱባቸው በማለት ትእዛዛ አስተላለፋ ተባለ አንድ የኑየር ተወላጅ ጀኔናር በአደረገው እርዳታ በሰላም ተመለሱ/በዚህ እንቅስቃሴ ላይ እንዳለን እኔም ተመታሁ ገደለነ ብለው ጥለውኝ ህደዋል ቤተሰቦቸና ፓሊስ አንስቶ ኮፐቲክ ወደተባለው ሆስፐታል ወስደው አስተኝተውኛል በሁለተኛው ቀን ስነቃ ከእጀ ላይ ግሊኮዝ አለ ልጆቸና ባለቤቴ ያለቅሣሉ ሰውነቴን ማንቀሣቀስ ስሞክር እንቢ ሲለኝ መመታቴን አወኩ ወደከፍተኛ ሆስፔታል ተላኩ ኩኩዮ ሆስፐታል ይባላል የተሰበረው እግሬ በጀሶ ታሰሮ ከ3ወር በኋላ ተመለስ  ተብየ የምራመድበት2 ክራንች ተቀብየ ተመለስኩ;ኬንያ ገንዘብ ነው ህግ ለአንተ ከለላ አይሆንም 3ወር ቆይቸ ቁስሉን ለማስፈታት ስህድ አሁንም ለ3ወር መታሼግ አለበት ተብሎ ድጋሜ ታሸጎ ተመለስኩ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ u.n.h.c.R፣ቢሮ ህድነ ቀደም ሲል የኔን ጉዳይ ያውቁት ስለነበር አድራሻኅ ጠፍቶነ ነበር ቦታ ተዘጋጅቶልህል ተባልኩ ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ  ከነቤተሰቦቸ ከአንድ ሆቴል ቤት አስቀመጡን ከዚህ ግቢ እንዳትወጣ ተባልኩ፣ትንሸ ወራት እንደቆየን3ኛ አገር ተገኝቶልሀልዴንማርክ ፈቃደኛ ከሆንክ ተዘጋጅ ተባልኩ  በክራንች ተደግፊ ከአይሮፓላን ተሣፈርኩ፣ወዲያው እንደደረስኩ ወደሀኪም ቤት ተወሰድኩ መዳህኔት ተሰቶኝ ተመለስኩ ከትንሸ ወራት ቆይቸ በራጅ አይተው ስብራቱ መዳኑን ሀኪሙ አረጋገጠልኝ፣በእጀ የነበረውን ምርኩዝ ትቸ መራምድ ቻልኩ የሚቀጥለው እርምጃ ምን ይሆን,

እረፍት ያጣው ህሊናየ ግን መዳህኔት አልተገኜለትም/

ተከፍሎ.ያላለቀ.እዳ፤ጉዞ.ወደ.ኤርትራ

በምንም.ተአምር ኤርትራ ምድር ህጀ እታገላለሁ ብየ አስቤም አላውቅ በወያኔና በሻቢያ መካከል ስድብና የጀግንነት ፍክክር ከመጨረሻ ጠርዝ ደርሶ ነበር እኔ ከምኖርበት አገር ዴንማርክ ድሮ በደርግ ዘመን ሻቢያንና ወያኔን ሲቃወም በራዲዎ አዳምጠው የነበረ ሰው እኔ ካለሁበት አገር መኖሩን ሰማሁ በአካል አላውቀውም  በአካል ተገናኜን ምን እናድርግ በሚለው ላይ ተስማምተን ተለያየን;በዚህ ዘመን ሻቢያም ተቃዋሚዋችን ሲፈላልጉ ንሮ ሱይድን የምትኖር የሻቢያ አንባሳደር ጋር በአካል ተገናኝተን ተነጋገርን በእለቱ ወስነን ትኬት ተገዝቶልን ጉዞ ወደአስመራ በረርን፤አስመራ ደረሰነ በክብር ተቀበሉን vip ማለት ነው፣አስመራ ከተማ3 ቀን ከቆየሁ በኋላ አብረን ከህድንው ጓደኛየ ጋር በጋራ ትግል መቀጠል አልቻልነም፣

ተለያየን ማለት ነው ከኮሎኔል ታደሰ ጋር ከዚያ በፊት አንተዋወቅም እንድንገናኝ ያደረጉት እነሱ ናቸው መኪና ተመደበልን ወደተከዜ ተጉዘን ተሰኔ ገብተን አደርን/ከምዕራብ ስሜን የጦር አዛዥ ከጀኔናር ተክሌ ጋር ተገናኜን በበነጋው ኩሎኔል ፍጹም ወዳለበት አሪና ተጉዘን በምሼት ገባን ኮሎኔል ፍጹም ተቀበለን ትንሸ እንደቆየን በመኪና  እያዞረ ገለጣ አደረገልን እነማን እንዳሉ ሁሉንም ማግኜት እንደምችል ተነግሮኝ ወደሱ ማደሪያ ቤት ተመለስነ በጣም ከመሼ በኁላ ተስፋየ ጌታቸው መጣ እኔ ከተኞሁበት ነበር የመጣው ሰላም አለኝ ተሰፋየ ነኝ ከምኝታየ ተንስቸ ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጥን ከተስፋየ ጋር ናይሮቢ ኬንያ እንተዋወቃለን ሱዳን መህዱን አውቃለሁ አስመራ መምጣቱን አላውቅም የድሮ ትውውቃችን በኔና በሱ ብቻ እንዲጠበቅ አድርገን ተለያየን በ92 ዓ.ም አስመራ ስንገባ ከአሜሪካና ከአውሮፓ የመጀመሪያወች ነበርን ማለት እችላለሁ ከኛ በፊት ከሱዳን አስመራ ገብተው መደራጅት የጀመሩ ነበሩ;ሁሉንም ማግኜት እንደምፈልግ ተነጋግረን እራት አብረን እንድንበላ ኮሎኔል ፍጹም ፈቀደ.ሁለት ፍየል አስገዝቸ እራት አብረን በላን ሁሉም በአሉበት የራሴን ድርጅት ልመስርት ወይስ አብረን እንታገል የሚለውን ሀሣብ አነሣሁ፣በሁሉም ማለት ይቻላል አብረን በውህደት እንታገል የሚለው ሀሣብ ዳብሮ ለኮሎኔል ፍጹም ቀርበ እናንተ ብቻ ሣትሆኑ ሌሎችም የጎሣ ድርጅቶች ይጠሩና ተመካከሩ ይህ እንዲሆን የኤርትራ መንግስት ይፈልጋል ይህንን ለማቀራረብ እየሰራን ነው በሚል የሀሣብ ስምምነት አደረግን የወረሞ ግንባር የሲዳማ ግንባር የሱማሌ ግንባር በያሉበት ተጠርተው መጡ ሚያአዝያ 10-11-12-92 ዓ.ም ለ3ቀን ጉባየ ተከሀዳ ይህ ጉባኤ ለኔ የሚጎፈንን ነበር ኢትዮጵያዊነቴን የገለጽኩበት የሀገሬን ውርደትና ስድብ ፊት ለፊት የሰማሁበት ነበር ስብሰባውን አቋርጨ ወጣሁ በምሣ ስአት አቶ የማነ መቶ ከኔ በጣገብ ተቀመጠ ምሣ አብረን በላን የሀሣብ ልውውጥ አደረግነ ተስማምተዋል በትግስት ከስብሰባው ግባ ተባልኩ ገባሁ ቀደም የነበረው ሀሳብ ተለውጦ ሁላችንም ቀዝቀዝ ብለን ጀመርነው እየጎመዘዘኝም ቢሆን ከ3ቀን በኁላ ከስምምነት ደርሰን ተፈራረምን.1ኛ በአማርኛ 2ኛ በትግርኛ 3ኛ በወሮሞ ኛ 4ኛ በአረብኛ 5ኛ በእንግሊዝኛ ተጽፎ ተፈራርምን ደብዳቤው እንዲበተን በየድርጅቱ ተወካዮች ደብዳቤ ይዘው እንዲህዱ ሲወሰን እኔ በተስፋየ ጌታቸው የተፈረመ የውክልና ደብዳቤ ተሰቶኝ ወደአውሮፓ ተመለሰኩ፤በአውሮፓና ወደ አሜሪካ አድራሻ እየጠየኩ የተሰጠኝን ደብዳቤ በተንኩ እኔ የተሰጠኝ ግዳጅ ነበር ወደአፍረካ ተጓዝኩ  ውጋንዳ ነበር የህድኩት ውጋንዳ በዘመኑ ቁልፍ ሰው ተብለው ከተመረጡት አንድ ሰው የዛሬው ዶክተር በዚያንጊዜ አቶ ካሣ ከበደ ነበሩ፣ውጋንዳ መኖራቸውን አስመራ ስለተነገረኝ በአካል ተገናኜኋቸው ከዚያ በፊት አላውቃቸውም ለመጀመሪያ ስንገናኝ አብሮኝ የነበረው የድሮ ኮሎኔል ከአስመራ መምጣቴን ነገራቸው ስሜን ጠየቁኝ አንተነህ በአስመራ እራዲዎ ቃለ ምልልሰ የሠጠህው አዳምጨሀለሁ በኛ መንግስት ጊዜ በምንስልጣን ነበርክ አላውቅህም አሉኝ እኔማ አባራችሁኝ በስደት ሱዳን ነበርኩ ይገርማል አነተ ነህ በርታ የሚል ሞራል ለገሱኝ ነገሩን ለሰስ ባለ አቀራረብ አነሣሁላቸው እኔ አሰመራማ አልህድም ከተቻለ ሀሣቡን አልቃዎምም የሚል መልካም ሀሣብ አገኜሁ ከአስመራ ይዤው የመጣሁት ስጋት እንደሰጋነው አይደለም፤ከ5ቀን ቆይታ በኃላ ወደ አውሮፓ ስመለስ ካናዳ የሚታተም ሀዋርያ የሚባል ጋዜጣና INDAN 0CEAN NEWS LETTER) የተባለ ጋዜጣ ዘግበውት አነበብኩ ማን እንዳስተላለፈው አላውቅም በዚሁ ዘመን ለፕሮፊሰር ጥላሁን ይልማ ስልክ አፈላልጌ አነጋገርኳቸው እኔ ለምትጠራኝ ጉባኤ የምመጣው የዓሉላ አባነጋን ሀውልት ለመስራት መቶ ሸኅ ብር እዤ እመጣለሁ ፐሬዘዳታችሁን አስፈቅደህ ጠይቀኝ የሚል ነበር ሀሣቡን ለተስፋየ ጌታቸው አወያየሁት ለሚመለከተው አቀረበው አንድ የኤርትራ ደህንነት ኮሎኔል ተመድቦ ጉዳዮን ይከታተል ነበር ደብዳቤ ይጻፋ ተባለ 3ገጽ ወረቀት በእንግሊዝኛ የተጻፈ ስጣቸው ብለው ላኩልኝ በፓስታ አሸጌ አደረሰኩ የተወከለው ኮሎኔል ወረቀቱ አልተመቸውም ቅሬታውን ገለፀልኝ፣ደብዳቤ ከላኩላቸው ሰወች አንድ ከሆላንድ አንድ ከእንግሊዝ ፈቃደኛ ሁነው ተነሱ አንዱ ቪዛ ሲከለከል አንዱ በቦታው ተገኙቶ Eppf የሚለውንም ስም  ያወጣው ይህዉ ኢትዮጵያዊ ዶክተር ነው፣ዛሬም እንግሊዝ አገር በህይወት አለ፣

አርበኞች ግንባር ከተመሰረተ በላ በውጭ አገር የማስተዋወቁ ፈተና፣

ለኢትዮጵያ ነፃነት ሻቢያ ይበጀናል ብሎ ወደሕዝብ እዞ ለመቅረብ የሚያስፈራበት ወቅት ነበር curent affirs) የተባለው.የሕዝብ መወያየ መድረክ ብዙ ሕዝብ አልነበረም በመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት ወጣቶች ጋር ተነጋግረን፣ወደመድረክ እንዲወጣ አስተዋጽዎ አድርገናል፣

1ኛ ኖቫ የተባለ ወጣት ፣

2ኛ እንደልቡ የተባለ ወጣት፣

እነዚህ 2 ወጣቶች ለምን ለሕዝብ በግለጽ ወተው አይናገሩም አሉኝ በአሁኑ ስአት አስመራ ጦር አለኝ ለማት ቀርቶ ከእነሱ ጋር መነጋገር ወንጀል ነው በተባለበት ስአት አይቻልም ነበር የሚል የኔ ሀሣብ፣ሁለቱ ወጣቶች ግን አደፋፍረው በቅዳሜ ቀን ለሕዝብ ማስታወቂያ ጠርተው ቤቱን እነሱ እየመሩ ጃናሞራ የተባለውን ዘፈን እያጫወቱ በክብር አስተናገዱኝ ትልቁ ችግር ምንድነው ለሚለው ጥያቄ የመኪና ችግር አለባቸው ነበር የኔ መልስ ተመካክረን ችግሩን እንፈታለን በሚል ተለያየን፣በሌላ ጊዜ በገቡት ቃል መሰረት ሰው መርጠው ገንዘብ አዋተው ሰው ልከዋል፣ለዚህም ግንባር curent affairs) ባለውለታ ነበር ማለት ያስደፍራል፣ያ ሁሉ ድካም ተዘንግቶ በተፈጠረው የሀሣብ ልዮነት ጥሩ ተሣዳቢና ጥሩ አሰዳቤ አዘጋጅቶ በቦታው ያልነበሩትን ሰወች ሰማን በሚል ቱማታ ከሀቅ ውጭ የሚደረገው ዘመቻ አስተማሪነት የለውም፣ለሀገርም ለትውልድም አይጠቅምም ስድብ በሀሣብ የመቸነፍ ምንገድ ነው፣እኔ የተቃወምኩት የመታገያውን ሜዳ ነው፣ሀሣቤም እውነት ነው ለሀገሬ የማይበጀውን ሁሉ አቅሜ  እስከፈቀደ ድረስ እገፋበታለሁ፣ለትውልድና ለሀገር በሚጠቅም ደረጃ ጊዜን ገንዘብን እውቀትን ጀግንነትን እናበርክት፣የሚለውን ምክሬን ከአክብሮት ጋር እለግሣለሁ  የተከበራችሁ አንባብያን እነዚህን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ምሁራን ለጉባየ የጋበዝነው በስብሰባው ይገኛሉ በሚል ታሣቢ አይደለም ትግሉን ወደሕዝብ ለማውረድ በሚደረግበት ወቅት የሚሰጡት አስተዋጽዎ አዲስ እንዳይሆንባቸው የሚለውን በማገናዘብ ነው፣በሁለት ወር ተገናኝተን በመለስተኛ ፐሮግራም በጋራ ለመታግል የተያዘው ቀጠሮ ሣይደርስ ትልቁ የባድሜ ጦርነት ፈነዳ የተለያየ ምክንያት ከመስጠት የዘለለ የጎሣ ድርጅቶችን ማሰባስብ አልተቻለም፣ከ6ወር ቆይታ በኁላ ጥቅምት 7ቀን 93 ዓ.ም ቀደም ሲል በተነጋገርነው መሰረት አራቱ ድርጅቶቸ አርበኞች ግንባርን መሠረቱ፣ለትግሉ መሰናክል ማነው የሚለው እንዳለ ሁኖ ለአርበኞች ግንባር መመስረት ትልቁን ሚና የተጫወተው ከሎኔል ፍፁም ነው፤እሱ ባያግዘኝ ንሮ የኔም ተልኮ በቀላሉ ባልተሣካም ነበር፣ይህን ቭዲዎ ይመልከቱ፣

በምዕራፍ 2 እንገናኝ ቸር እንሰንብት ይቀጥላል

መልኬ መንግስቴ ነኝ

 

 

 

3 Comments

  1. Where were you before ,you are coming to late.We the Ethiopian people why we are jealous for each other and for that poor country.You was try but you cnnot fix just give to them and they will try.

  2. የአክብሮት ሰላምታን ለአቶ መልኬና ለእናተም ጭምር ደንበኛችሁ የአቶ መልኬ ጽኀፍ ጨዋነት የተላበሰ በመሆኑ ደስ የሚል ብዕር ነው እናተም ለስድብ ቦታ ባትሰጡ መልካም ነው ደንበኛችሁን አመስግኑልኝ

  3. የአቶ መልኬ አባት ስመ ጥሩው የቤገምድር አርበኛ በሞቱ ጊዜ የነበረውን የባህል የአባቶቻችን ገድል ስመለከት ይህን ማስታወሻ ለአናተ መላክ አሰብኩ በእኔ እምነት ትውልድ ሊያው ይገባል ከሚል ድምዳሜ ደርሻለሁ ካመናችሁበት ሕዝብ ቢመለከተው ምንይመስላችሁአል all dear Brother That is the Real history
    Youtube Melake Genet Mengiste Abetew.com
    great

Comments are closed.

Previous Story

Hiber Radio: አሜሪካ ሶማሊያ ለሚገኘው የኢሕአዴግ እና የጅቡቲ ጦር የመረጃና የስለላ ስልጠና እየሰጠች መሆኗ ታወቀ – ሕንድ ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ማንን እንደምመርጥ ተቸግሬያለሁ አለች (ሌሎችም ዜናዎች አሉ)

Next Story

የሕወሓት መንግስት የታጠቁ ኃይሎቹን እና ካድሬዎቹን በማሰማራት በአርማጭሆ ሕዝብ ላይ ሰቆቃ እየፈጸመበት እንደሚገኝ ተዘገበ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop