August 18, 2015
2 mins read

በቤንሻንጉል ጉሙዝ የተገደሉት 11 ሰዎች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ነዋሪዎች ተናገሩ

ኢሳት ዜና :-ከአለፈው ምርጫ ጋር ተያይዞ ፣ የአካባቢው ህዝብ የስርዓቱ ደጋፊ አይደለም፣ በምርጫውም ለመሳተፍም ሆነ ከመንግስት ጎን ለመቆም ፍላጎት አላሳየም በሚል የበቀል እርምጃ እንደተወሰደባቸው የአካባቢው ተወላጆች፣ የልዩ ሃይል አባላት በወሰዱት የጭካኔ እርምጃ እስካሁን በመንጌ ወረዳ 11 ሰዎች መገደላቸውን ገልጸው፣ ግጭቱ ወደ ዳቡስ አካባቢም የተዛመተ በመሆኑ የሟቾቹ ቁጥር ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።

በመንጌ ከተማ አካባቢ በነበረ የአርብ ቀን ገበያ ላይ በተወሰደው አሰቃቂ እርምጃ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በተለይም ወደ ሜዳ ኦዶ ከተማና ዳቡስ አካባቢ ወደ ሚገኙ መልስተናኛ ከተሞች በሸሹት ግለሰቦች ላይ እርምጃ ተወስዷል።

በአካባቢው አሁንም ውጥረት ሰፍኖ እንደሚገኝ ነዋሪዎች ገልጸዋል። በአካባቢው የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአለፈው ምርጫ እንዳይሰተፉ የተከለከሉ ሲሆን፣ ህዝቡም ይህን ተከትሎ በምርጫው ላለመሳተፍ አቋም ወስዶ ነበር።

ኢሳት ታጠቂዎች በወሰዱት እርምጃ 12 ሰዎች መገደላቸውን፣ ከሟቾቹ ውስጥ 5ቱ ህይወታቸው ያለፈው እስር ቤት ከተወሰዱ በኋላ በምግብ ተመርዘው መሆኑንና 56 ሰዎች በመንጌ ወረዳ በአሶሳ ሆስፒታል በህክምና ላይ መሆናቸውን እንዲሁም 54ቱ ሰዎች መታሰራቸውን፣ የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄን በመጥቀስ ዘግቧል።

Previous Story

የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ እድር ላይ ጥያቄ አነሳህ ተብለው ታሰሩ

Next Story

በ800 ሜትር የመሀመድ ውጤት ተሰረዘ!

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop