Hiber Radio: ፕ/ት ኦባማ ኢህአዴግና አማጽያኑን እንዲሸመግሉ መጠየቁ፣ አምንስቲ እንግሊዝ ለኢትዮጵያው አገዛዝ አፈና መጠንከርን ተጠቃሽ አደረገ፣ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ጦርነት መክፈት የፈጠረው መነቃቃት፣ እስራኤላዊው ትውልደ ኢትዮጵያዊው በሐማስ እጅ መውደቅ የፈጠረው ተቃውሞ፣ የጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ እና ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ቃለ መጠይቅ፣ የመን ሰንዓ ኤምባሲ ፊት ለፊት የወደቁ ኢትዮጵያውያን ያሉበት ስቃይ እና ሎሎችም

/
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ ሐምሌ 5 ቀን 2007 ፕሮግራም

<…የሌላው ሰው ህመም ህመማችን ሊሆን ይገባል። እንደ አሜሪካ ለሰብዓዊ መብት ያገባኛል የሚል መንግስት ያገባኛል ለሚለው ነገር መቆም አለበት ብዬ አስባለሁ…ዘርን ሀይማኖትን ያደረገ ክፍፍል ሳይኖር አንድ ላይ ለፍትሕ፣ለዕውነት ፣ ለዲሞክራሲ መቆም ብንችል ትልቅ ለውጥ ይመጣል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም…> ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ ከሰጠችን ቃለ መጠይቅ ላይ ከተናገረችው (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…በሎስ አንጀለስ የተደረገው የአርበኞች ግንቦት ሰባት የገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ ነበር ። ያልተመቻቸው ሰዎች እንኳን አስቀድመው ትኬቱን በመግዛት እኛ ራሳችን ከጠበቅነው በላይ የተሳካ እንዲሆን…> አቶ ሳምሶን ደበበ በሎስ አንጀለስ የተደረገው ገቢ ማሰባሰቢያ አስተባባሪዎች አንዱ ከሰጡት ቃል የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…እስክንድር ከታሰረ አራት ዓመት ሊሞላው ሁለት ወር ብቻ ነው የቀረው። እስክንድር ብቻ ሳይሆን እስክንድር የታሰረለትም ዓላማ አብሮ ይፈታ …ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሚደረገውን ነገር አያውቁትም ብዬ አላስብም። ማነው ዓመታዊ ሪፖርት እያወጣ ሲያወግዝ የነበረው? ኦባማ አይደለም ኢትዮጵያ መሄድ ከፈለጉ … >

የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ንግግር የተወሰደ ቀሪውን ያዳምጡት

< …እነዚህ ወገኖቻችን የመን የሚገኘው ኤምባሲ በር ላይ ወድቀው በረሃብ፣ በሙቀትና በዝናብ እየተሰቃዩ ነው። ዓለም አቀፉ የስደት ተመላሾች ማህበር(አይ.ኦ.ኤም) ካምፕ ወዳለበት ከሰንዓ ለመውጣት ፈቃድ ለማግኘት አማጽያኑን ስንጠይቅ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን አምጡ ተባልን። ሄደው ኤምባሲ ሲጠይቁ ከቀሩት ሁለቱ አንዱ ኢትጵአዊ መሆናቸውን አላረጋገጥንም ስላለ…ሁሉም ለነዚህ ወገኖቻችን ሊደርስ ይገባል..> ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት በየመን ሰንዓ አገራችን እንገባለን ብለው በ<<ኢትዮጵያ>> ኤምባሲ በር ላይ እየተሰቃዩ ስላሉ ከሃምሳ የበለጡ ወገኖቻችን በተመለከተ ከተናገረው (ሙሉውን ያዳምጡት)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሸንጎ ‘በአማራው’ ላይ ያነጣጠረውን የዘር ጥላቻ አወግዛለው አለ

<…ጋዜጠኛ ሀብታሙ ምናለ ርዮት የተፈታች ዕለት ከቤቱ በደህንነቶች ታፍኖ ተወስዶ ዛሬ ግን ጣቢያ ይገኛል ፍርድ ቤት አልቀረበም…> ስለ ጋዜጠኛው መታፈን ምስክር ከተናገረው(ሙሉውን ያዳምጡ)

የደቡብ ሱዳን አራተኛ የነጻነት ቀኗ እና ሰላም የራቀው ውስጣዊ ሽኩቻ(ልዩ ዘገባ)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ፕሬዝዳንት ኦባማ ኢህአዴግን ከተቃዋሚዎች ጋር እንዲሸመግሉ ጥሪ ቀረበ

አንዳንድ ባለስልጣናቱ በዕርቀ ሰላም አያምኑም ተባለ

አምንስቲ የኢትዮጵያው አገዛዝ ዜጎችን ለመሰለሉ እንግሊዝን ተጠቃሽ ሊያደርግ ይችላል አለ

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ጥቃት መሰንዘር በሕዝቡ ውስጥ መነቃቃት እየፈጠረ ነው

የታክስ ጫናን በመቃወም በአዲስ አበባ ስጋ ነጋዴዎች የስራ ማቆም አድማ መቱ

የኢትዮጵያዊው ቤተ እስራኤላዊ በሐማስ እጅ መውደቅና ደብዛው መጥፋት በወገኖቹ ላይ ቅሬታ ፈጠረ

በወያኔ ላይ የተከፈተው ውጊያ ወደ አርማጭሆ መሸጋገሩን ግንባሩ ገለጸ

ኤርትራ የአፍሪካ ቀንድ የራስ ምታት ሳትሆን የፕሮፖጋንዳ ሰለባ መሆኗን ኢትዮጵያዊው ምሁር አውሮፓ ላይ ገለጹ

በውጭ የሚገኙ የነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች የቀሩትም ጋዜጠኞችና ጦማሪያን እንዲፈቱና ጸረ ሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ ጠየቁ

ፌስ ቡክ የኢትዮጵያዊውን የግብረ ሰዶማዊ ድህረ ገጽ አካውንት መዝጋቱን አስታወቀ

<<ማንነቴን በመደበቄ ለፌስ ቡክ ሰለባ ሆኜያለሁ>> በአሜሪካ የሚኖረው ድህረ ገጹ የተዘጋበት ግለሰብ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

1 Comment

  1. የ አመቱ ምርጥ ቀልድ….. ፕሬዚደንት ኦባማ አማጺያንንና መንግስትን እንዲሽመግሉ መጠየቁ…….ቂቂቂቂቂቂቂቂ

Comments are closed.

Share