ሸንጎ ‘በአማራው’ ላይ ያነጣጠረውን የዘር ጥላቻ አወግዛለው አለ

ጋዜጣዊ መግለጫ

የካቲት 4፣ 2006

ከጅምራቸው ሕወሃትና በዙሪያው ያሰባሰባቸው ተለጣፊ የዘር ድርጅቶች ሥልጣንን ለመቆጣጠር ሆን ብለው ይዘው የተነሱትና ያካሄዱት የዘር ፖለቲካ መሠረት ያደረገው ‘የአማራውን’ ሕዝብ የሚወነጅል፣ የሚያጥላላና የሚያንቋሽሽ ብሎም ለጥፋት የሚዳርግ እንደሆነ የሚየሳዩ ከበቂ በላይ ማስረጃዎች ማቅረብ ይቻላል። ይህንንም ዓላማቸውን ለማስፈፅም ከተጠቀሙበት መንገድ ዋናው የዚህን ሕብረተሰብ መሪዎችና የቅርስ ማዕከሎች ሚናና አስተዋፅዖ የሚያንኳስሱና የሚያዋርዱ የፈጠራ ታሪኮችና ወሬዎችን መፈብረክና ማሰራጨትን ያጠቃልላል።

በቅርቡ ያለፉት መለስ ዜናዊና ጓደኞቻቸው ከሰላሳ ዓመታት በላይ በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ‘የአማራውን’ ሥም አጥፍተዋል፣ ጥላሸት ቀብተዋል፣ የሚያዋርዱና የሚያጥላሉ አባባሎችን ተጠቀመዋል፤ ለተለያዩ ዘውግ ልሂቃኖችም ‘አማራዎችን’ ለዘመናት ከኖሩበት ቀዬአቸው፣ መሬታቸው፣ ንብረታቸውና ቤታቸው እንዲያፈናቅሉ የሚያነሳሱና የሚገፋፉ መልክቶችን ሲያስተጋቡ ቆይተዋል። በቀደሙት ብዙ ዓመታት የሕወሃት/ኢህአዴግ መሪዎች ‘የአማራውን’ ሕዝብ በማፈናቀልና ለይቶ በማጥቃት የተፈፀመውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፤ ከአካባቢና ከክልል ጉዳይ ጋር ብቻ የሚያያዝ በማስመሰል ራሳቸውን ከሃላፊናትና ከተጠያቂነት ነፃ ለማውጣት ሲሞክሩ ቆይተዋል።

በቅርቡ ‘በአማራው’ ክልል ምክትል ፕሬዚደንት በአቶ አለሙ መኮንን የተሰነዘረውን ለሰሚው የሚከብድ ሕዝቡን የሚያንቋሽሽ ቅጥ ያጣ ውንጀላና ዘለፋን ሽንጎው በጥብቅ ያወግዛል።በዚህ ድርጊቱም ያሳየው ለሕዝቡ ያለው ዝቅተኛ አስተያየትና ለሰብዓዊ ክብሩም ያለው ጥላቻና ንቀት በማንኛውም መለኪያ ከወንጀለኛ ሰው የማይተናነስ እንደሆነ ነው፤ የዚህ አይነቱ ተጋባር በማንም ይቅር ሊባልም ሆነ ሊረሳ የማይችል ነው። ይህ የዝቅተኛነት ስሜት የተጸናወተው ግለሰብ ቀድሞ በሕወሃት መሪዎች በተጠነሰሰው አስቀያሚና አፀያፊ የታሪክ ተውኔት የወቅቱ ተዋናይ የመሆን ዕድልን አግኝቷል።

በእኛ ዕምነት እንደዚህ ያለ መዘላበድ ሃላፊነት የጎደለው ብቻ ሳይሆን ሁኔታዎች እንደ ዘር ማጥፋት ላሉ ያልታሰቡ እልቂቶች እንዲያመሩ አስተዋፅዖ ሊያደርግ የሚችል አደገኛ ተግባር በመሆኑ፤በሁሉም የሲቪክና የፖለቲካ ቡድኖች፤ በታወቁ ግለሰቦችና፤ በሃይማኖት መሪዎች ሊወገዝ የሚገባው ነው እንላለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስምምነት ከተደረገባቸው አገራት ውጪ የሚደረግ ሕገወጥ ጉዞ መቆም እንዲቆም ማሳሰቢያ ሰጡ

ሸንጎው ለዚህ አሁን ለደረስንበት እጅግ አሳፋሪ ሁኔታና ጥፋት ሁሉ በዋነኛነት ተጠያቂ መሆን ያለበትና ሃላፊነቱን መውሰድ የሚገባው የሕወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ነው ብሎ ያምናል። ይህ ዓይነቱ ድርጊት እንዲፈጠርና እንዲካሄድ ምክንያት የሆነው በጥቂት ዘረኝነት በተጠናወታቸው ግበሰቦችና ቡድኖች ቁጥጥር ሥር ያለው የፖለቲካ ሥርዓት ካልተወገደ በቀር ተመሳሳይ ሁኔታዎች መቀጠላቸው አያጠራጥርም።

በመጨረሻም በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፉ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማሕበራት በመሐከላቸው ያለውን አነስተኛ ልዩነቶች በማቻቻል፤ ጠንካራና ሠፊ የጋራ ትብብር በመፍጠር ኢትዮጵያውያንን እርስ በርስ በመከፋፈልና በማጋጨት ስልጣኑን በማራዘም የተካነውን አሰከፊ አምባገነን አገዛዝ፤ ለማስወገድና በምትኩም አንድነቷ በተከበረ ኢትዮጵያ ስር ሁሉንም እኩል የሚያሳትፍ ህገመንግስታዊ ዴሞክራሲአዊ ሥርዓት ለመገንባት ባንድ ላይ እንዲሰሩ በድጋሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በእውነተኛ ልጆቿ ሃይል ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!

6 Comments

  1. ኢትዮጵያ……በእውነተኛ ልጆቿ ……ትኖራለች! i have question here. who are them እውነተኛ ልጆች እና ውሸተኛ ልጆች? this is the main problem why unity cannot come again in ethiopia. some are considerring themselves as they are the only ethiopians and try to bost themselves. as far as i know all are ethiopias and proud of it. if you cannot accept that and deny the national issue, then they will go what they in hand like ertria did before.

    • You can be one true Ethiopiawi. To be that, all it requires is your willingness to be one. Meaning, that is your choice. An example of false Ethiopiawi are meles and his mercenary friends. They are not Ethiopians. They do not serve Ethiopia’s interest. We have witnessed that time and again. They work for someone else. We as a people must figure out for whom. It may be for Westerners, China, India, the Arabs (the dark age Saudi Arabia, Egypt (do not be deceived with all this fugera about the GERD dam. Egypt will come out as a winner eventually) Sudan, or our new neighbor in the mereb sea. Meles and his cronies are not for us; they are against us. That is the classic example of false Ethiopians. You do not want be that, do you?

    • Ye Ethiopia yewushet lijochin yematawiqacew kehon “those who are banda woyanes ” or ye shabiya telalakiwoch nachew. They always stands for shabiyas’ interest.

  2. I have no interst to asulat people. However. we have brought up in a society where one insult the other. what is special of this. Haven’t u ever heard when it said that qemant came from tree, Agew libu zetegn and oromo is such and such. Ato Aleminaw is a man who called a spade spapde. period

  3. The Shengo stand Amhara then if they are concerned that much for one ethnic group. I have never heard them complaining for others. Why hiding behind citizenship Ethiopia then. Just come out as Shengo Amhara and let’s compete against TPLF.

  4. Oboo mslohal! hids bitbal yet lithead new? Ewuet yemilewun min yahl indemtfera awukenal. Ewunetn yemitela meheaja yelewum!

Comments are closed.

Share