በአፋር ክልል ወጣቶች ለውትድርና በግዴታ እየታፈሱ ነው

(ፎቶ ፋይል)ከአኩ ኢብን አፋር

በአፋር ክልል የህዝባዊ ወያነ ሐሪነት ትግራይ መንግስት የአፋር ህዝብን ደካማ ጎኑን በመጠቀም ወጣቶችን ለውትድርና እያፈሰ ይገኛል።

አለም አቀፍ የምግብ ተረድዖ ድሪጅት በእንግለዘኛ ምህጻሩ WFP ( worlid food program ) ለኢትዮጲያ ህዝብ የሚሰጠው የእርዳታ እህል ለውትድር መደልያ በመጠቀም በአፈር ክልል በብዙ ወረዳዎች እርዳታን ለማገኘት ከአንድ አባወራ ቢያንስ አንድ ሰው ለውትርና መመዝግብ አለበት።

የወያነ መንግስት የመዕራባዊያን ድጋፍ ላለማጣት የገዛ ወታደሮቹን በሰላም አስከባሪነት ሽፋን በሶማሊያ እና በደርፎር በማሰማራት እየፈጃቸው መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አፈሳው እየተካሄደ ይገኛል።

በአፋር ክልል 80% የሚሆን ህዝብ ከውጭ በሚገኘው እርዳታ የሚተዳደር ሲሆን ወያነ ይህን ደካማ ጎናቸውን በመጠቀም እርዳታ ለማገኘት አንድ ሰው ከአንድ አባወራ ለውትድሪና ሰልጠና መመዝግብ አለበት ይላል።

በአፋር ክልል ይህ ህግ ወጥ ድሪግት ተግባራዊ የሚሆነው በአብደፓ የአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ መሪነት ስሆን በየቀበሌው አስተዳደሮች አማካኝነት ትዕዛዙ ወደ ህዝብ እንዲወርድ እየተረገ ይገኛል።

በአፋር ክልል ባሉ በ32 ወረዳዎች ይህ ጉዳይ ወቅታዊ እና አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  “አሸባሪው ሕወሓት የሚፈጽመው የሰብዓዊ ድጋፍ የማደናቀፍ ድርጊት በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሊወገዝ ይገባል” ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

1 Comment

  1. ኢትዬጵያ ሃገራችን በታሪኳ እንደዚህ አይነት የቆሸሸ እንደዚህ አይነት ውርደት እንደዚህ አይነት የብሄር ረገጣ እስካሁን አላየሁም ነበር እንደዚህ አይነቱን አሳፋሪ ልጂህን ለወታደርነት የሌላን ባአድ አገር ከጠላት እንዲከላከል ተብሎ ልጅህን ለሞት ካልገበርክ በልተን ለምናራው እርቧቸው ምግብ ባሉ ልጅህን ለሞት ገብርና እንካ ምግብ ማለት እጂግ በጣም አሳፋሪም አሳዛኝም ነው : ለመሆኑ ከአምባገነኖች መች ምቾት ይኖርና!

Comments are closed.

Share