በአዲስ አበባ ከተማ ዉስጥ ማንኛዉም አዲስ የእምነት ተቋም እንዳይገነባ መመርያ ወጣ

አቡበከር አህመድ እንደዘገበው:-

መንግስት በሴኩላሪዝም ስም ህብረተሰቡን በተለይ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከእምነቱ ለማስወጣት የሚያደርጋቸውን ጥረቶች አጠናከሮ የቀጠለ ሲሆን የዚህ እቅድ አንደ አካል የሆነውን ድርጊቱን ማንኛዉም አይነት የእምነት አዲስ ተቋማት በአዲስ አበባ ከተማ ዉስጥ እንዳይገነቡ በሚል መመሪያ ማዉጣቱን ምንጮች አስታዉቀዋል።

በየትኛዉ እምነት አማኞች ፈጣሪያቸውን በአንድነት የሚያመልኩበት ቦታና የእምነቶቻቸውን ጥሪ የሚያደርጉበት ቦታ የእምነት የእምነት ተቋማቸዉ ሆኖ እያለ ከተማዋ እጅጉን እያሰፋችበት በሚገኘው በዚህ ወቅት ላይ ይህ አይነቱ ወሳኔ መተላለፉ መንግስት ህብረተሰቡን ከእምነቱ ለማራቅ ያለውን ፍላጎት የሚያሳይ ነው ተብሎ እየተተቸ ነው::

ዉሳኔው ሌላ መመሪያ እስኪመጣ ድረስ እንዲሰራበት የተላለፈ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በቅርቡ በተለያዩ እምነቶች ለእምነት ተቋም መገንቢያ ተብለው የተከለሉ ቦታዎችን መንጠቅ እንደተጀመረም ምንጮች አካተዉ ገልፀዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰላም በር ተዘግቶ የተደረገውን 6ኛ ፓትርያሪክ ምርጫ እንደማይቀበል የዲሲ ቅ/ገብርኤል ካቴድራል አስታወቀ

1 Comment

  1. ትድኩ ቀርቶ በቅቱ በኮነነን !! ክክክ

    ባልዉስ መች በነታነት ተተቀምንብት

    በቅድመያ ወያነ ይውደም!!!

    የገነባል አይዞን !

Comments are closed.

Share