በድቡብ ሱዳን አራት ኢትዮጵያውያን በጥይት ተመቱ

በደቡብ ሱዳን በዋና ከተማዋ ጁባ አንድ ወንድና አንድ ሴት ሲገደሉ ሁለት ሴቶች ግን በጠና ቆስለው ወደ ኢትዮጵያ መወሰዳቸውን ኢሳት ወኪሎቹን ጠቅሶ ዘገበ። የሁለቱም ሟቾች አስከሬንም በኢትዮጵያውያን እርዳታ ወደ ኢትዮጵያ መሄዱ ታውቆል:: ሰዎቹ በምን ሁኔታ እንደተገደሉና እንደቆሰሉ
እንዲሁም ጥቃቱን ያደረሱትን ወገኖች ዝርዝር ለማወቅ አልተቻለም ያለው ኢሳት በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በኢትዮጵያውያን የሚደረገውን ግፍና እንግልት ከመከታተል ይልቅ በዶላር ጥቁር ገበያ ምንዛሪ መሰማራቱን የገለጸው ወኪላችን ፣ የቀድሞ የህወሃት ባለስልጣናት በጁባ ከተማ የሚያራምዱትን የቢዝነስ ተቋምና በጋምቤላ በኩል የሚያመጡትን የጤፍና የተለያየ ሸቀጣሽቀጥ ንግድ ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚያቀርቡትን አቤቱታ እንደማይሰማ ተናግሯል። ለህወሃት አባሎች ህጋዊ የመኖረያ ፈቃድና የንግድ ፈቃድ ለማስወጣት የጁባ ባለስልጣናትን ደጅ የሚጠናው ኢምባሲው ምርቶችን ወደ ደደቡብ ሱዳን በማስገባት በኩል ወኪል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ጠቅሷል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በአዲስ አበባ የካራሎ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ በፖሊስ ላይ ተኮሰ

2 Comments

  1. u are right we are living in south sudan your correspondent is correct. Ethiopia embassy is working for” his own people” they don’t bother for other Ethiopian citizen. They are involved in different business. I remember one gay from tigray he was conductor(taxi redat) and broker after two month he got land in gambella, got loan from development(Limat) bank now he is rich. so they are helping and working peoples like him not for poor Ethiopian citizen.

Comments are closed.

Share