December 2, 2014
1 min read

በድቡብ ሱዳን አራት ኢትዮጵያውያን በጥይት ተመቱ

በደቡብ ሱዳን በዋና ከተማዋ ጁባ አንድ ወንድና አንድ ሴት ሲገደሉ ሁለት ሴቶች ግን በጠና ቆስለው ወደ ኢትዮጵያ መወሰዳቸውን ኢሳት ወኪሎቹን ጠቅሶ ዘገበ። የሁለቱም ሟቾች አስከሬንም በኢትዮጵያውያን እርዳታ ወደ ኢትዮጵያ መሄዱ ታውቆል:: ሰዎቹ በምን ሁኔታ እንደተገደሉና እንደቆሰሉ
እንዲሁም ጥቃቱን ያደረሱትን ወገኖች ዝርዝር ለማወቅ አልተቻለም ያለው ኢሳት በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በኢትዮጵያውያን የሚደረገውን ግፍና እንግልት ከመከታተል ይልቅ በዶላር ጥቁር ገበያ ምንዛሪ መሰማራቱን የገለጸው ወኪላችን ፣ የቀድሞ የህወሃት ባለስልጣናት በጁባ ከተማ የሚያራምዱትን የቢዝነስ ተቋምና በጋምቤላ በኩል የሚያመጡትን የጤፍና የተለያየ ሸቀጣሽቀጥ ንግድ ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚያቀርቡትን አቤቱታ እንደማይሰማ ተናግሯል። ለህወሃት አባሎች ህጋዊ የመኖረያ ፈቃድና የንግድ ፈቃድ ለማስወጣት የጁባ ባለስልጣናትን ደጅ የሚጠናው ኢምባሲው ምርቶችን ወደ ደደቡብ ሱዳን በማስገባት በኩል ወኪል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ጠቅሷል።

2 Comments

  1. u are right we are living in south sudan your correspondent is correct. Ethiopia embassy is working for” his own people” they don’t bother for other Ethiopian citizen. They are involved in different business. I remember one gay from tigray he was conductor(taxi redat) and broker after two month he got land in gambella, got loan from development(Limat) bank now he is rich. so they are helping and working peoples like him not for poor Ethiopian citizen.

Comments are closed.

Previous Story

Hiber Radio: በመስቀል አደባባይ ለተጠራው የአዳር የተቃውሞ ሰልፍ የአደባባይ ቅስቀሳ ይጀመራል፤ ሁበር በኔቫዳ ታገደ

Next Story

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop