June 30, 2014
5 mins read

ይሉኝታ ቢሱ ወያኔ በሚኒሶታ ቅሌቱን ተከናነበ

ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም በአላሙዲ የሚደገፈው የወያኔ ቡድን የሚኒሶታን ሕዝብና ሌላውን ኢትዮጵያዊ ለማደናገር በሚኒሶታ ጠቅላይ ግዛት በሴይንት ፓውል ከተማ በሚገኘው ኮንኮርዲያ ዩኒቨርሲት እስፖርት ሜዳ ላይ ባዶ  እስታድየሙን በመያዝ ቅሌቱን ተከናንቧል። ሕዝብን በመፍረት የስታድየሙን ዙሪያ በአረንጓዴ፣ ብጫ ፣ ቀይ ባንድራ  ሰቅለው ነበር። ለተቃውሞ የወጣውም ሕዝብ በአገር ቤትና በወያኔ ቤተክርስቲያኖች የሚጠቀሙበትን ወያኔ በባንድራችን  ላይ የለጠፈውን የሴይጣን ምልክት ያለበትን ባንድራ አለመጠቀማቸውን በማየት በኢትዮጵያ ባንድራ መቀለድ አይቻልም፤ በባንድራ ማታለል አትችሉም። ወያኔ ይህ ባንድራ አያውቅም፣ ይህን የኢትዮጵያን ባንድራ(አረንጓዴ፣ ብጫ፣ ቀይ ቀለማት  ብቻ ያለበትን ሳንደቅዓላማ) ለሁሌም ተጠቀሙ በማለት ተቃውሞና ማሳሳቢያ ሰጥቷል። በመኪና ማቆሚያ ከዚያም በሽቦ  አጥር እንዲሁም በለመዱበት የፍራቻቸው መከለከያ በሆነው ፖሊስ በውጭና በውስጥ የተከበበውና የተጀበው የኮንኮርዲያ  ዩንቭርሲቲ ስታድየም ወያኔዎች ይበልጥ ከሕዝብ ወለፈን እንዲርቁ ረድቷል።  ወያኔ በኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ላይ ያደረገውን የክፍፍልና በስፖርት ስም በሚኒሶታ ለማካሔድ  ያሰባውን ድርጊት የሚቃወመው ሕዝብ የወያኔና የአላሙዲ ገንዘብ ተቀባዮች ወደሚጫወቱበት ሜዳ ድረስ በመሄድ  ተቃውሙን በመፈክር ፣ በዝማሬና በጩሃት አሳምቷል። በወቅቱ ሕዝቡ ካሰማቸውና ከያዛቸው መፈክሮች ጥቂቶቹ ፡-

  • ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
  • Long Live Ethiopia !!!
  • ዘረኝነት ይቁም !
  • Stop Tribalism!
  • Free Tsegaye Debteraw
  • Free Eskender Nega
  • Free Andoalem Arage
  • Free Rhiot Alemu
  • Free Aberash Berta
  • Free all political prisoners in Ethiopia
  • Stop Killing Ethiopians
  • Stop Arresting Journalists
  • Stop Genocide in Ethiopia
  • We oppose recent killings of Oromo students in Ethiopia
  • Stop selling Ethiopia’ s land for Arabs and others
  • ሕዝብ ማፈናቀሉ ይቁም
  • በደም ገንዘብ ስፖርት ማካሄድ አይቻልም
  • በእስፖርት ስም የኢትዮጵያ ሕዝብ አይታለልም
  • ሚኒሶታ ለሕዝብ ጠላት መሸሸጊያ አትሆንም
  • አንድ ነን አንከፋፈልም
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሸንፋል
  • በባዶ ስታደየም ጫወታ የለም። ወያኔን ሕዝብ እንደማይወደው ከዚህ ተማሩ
  • እናንት ተጫዋቾች ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን ተሰለፋ
  • የደም ገንዘብ ይቅርባችሁ

ከመዝሙሮቹ ውስጥ፡-

  • አትነሰም ወይ አትነሰም ወይ ይሕ ባንድራ ያንተ አይደለም ወይ
  • እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም የደፈረሽ ይውደም

ሰልፈኛው በ4፡30 ፕም ላይ በሱተር ታርጌት ተሰብስቦ ወደፊት እቅድ ወጥቶ ተከታታይ ሰልፎች እንዲካሄዱ ወሰኖ  የሚኒሶታ ህዝብ የወያኔን ስታድየም ባዶ በማደረጉ ምስጋና አቅርቧል። በስብሰባው የተገኘው ሰልፈኛ በሚኒሶታ የሚገኙት  ለሕዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ከእነዚህ የወያኔ ከፋፈይ ቡድኖች ጋር በማንኛውም ጉዳይ ትብብር እንዳይደርግ  በአክብሮትና በወያኔ እየተበደለ ባለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ጠይቋል። ዘረኞቹ መገለል ይኖርባቸዋል።ወደፊት  በሚካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች የሚኒሶታ ሕዝብ እንዲገኝ በሚኒሶታ የተቋቋመው ግብረ ኃይል ጥሪውን በድጋሚ ያቀርባል።
በሚኒሶታ የተቋቋመው ግብረኃይል

 

 

2 Comments

  1. Wayana yanesawale zaranenatene atebekane enewagalane wayana laba nawu wayana b ethio laye eyadarasawu yalawu gefe makome alabate

  2. Thank you the Zehabeshe for the information. Ethiopians in Minnesota thank you for your great job making Concordia University stadium empty where Woyane is playing to divide Ethiopians. After I saw this article, I went to Concordia stadium to check the truth about the article. I saw 20( 1 m X 1 m = 1 square meter) Ethiopian flag without woyane’s sign and 7 US flag around the stadium. That is aimed to cheat Ethiopians with the flag that woyane does not accept. Two teams were playing without any audience. Some guys walking inside and outside the stadium wearing black eyeglasses to hide themselves. One Ethiopian told me that woyanes are giving $100 freely to open shop and sell items inside the stadium. They got the reply ,how can we open shops in an empty stadium? That is the way to go. These, dividers should be alienated and carry an empty stadium. Concerned Ethiopians are recording who is allying with them and working to them. That will be posted soon for the public.

Comments are closed.

Previous Story

ዐማራውም በደል አልመረው አለ! ጠላቶቹም የላም አሸናፊ ሆኑ!

31813
Next Story

የኢትዮጵያ የቀድሞ ዘመናዊ የጦር ሰራዊትን ታሪክ ሳንዘክር ስለ ኢትዮጵያ ማውራት አንችልም

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop