የወታደራዊ መኮነኖች ቅነሳ?! ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው!

ህወሓቶች ከትግራይ የሚቀነሱ ወታደራዊ መኮነኖች ሲኖሩ ከኦሮምያ፣ ደቡብና አማራ ክልሎች ደግሞ ይጨመራሉ የሚል መረጃ ያስደነገጣቸው ይመስላል። በዚህ መረጃ የደነገጠ የህወሓት ካድሬ ካለ በትክክል ስለ ህወሓት መረጃ የለውም ማለት ነው።

በወታደራዊ መኮነኖች ቁጥር መቀነስና መጨመር ጉዳይ ሙያዊ ትንታኔ መስጠት አስፈላጊ ይመስለኛል። ምክንያቱም ወታደራዊ መኮነንነት ማዓርግ እንጂ ሹመት አይደለም። የራሱ የሆነ ወታደራዊ ዲሲፕሊንና ሳይንስ አለው። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ አስተያየት ለመስጠት የተሟላ ሙያዊ መረጃ ሊኖረኝ ይገባል። አሁን የምችለው ሙያዊ አስተያየት ሳይሆን ፖለቲካዊ አስተያየት መስጠት ብቻ ነው። በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የብሄር (ወይ የክልል) ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ ሳይሆን የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ ነው።

 

(ወታደራዊ ማዓርግ የብሄር ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ መሆን አለበት ብዬ አላምንም። ልምድና ብቃት ያለው፣ ለደረጃ መኮነንነት የሚመጥን ስብእናና ዕውቀት ያለው እንዲሁም ለሀገሩ ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ፣ አካላዊና አእምሮአዊ ብቃት ያለው፣ ሁሉ ወታደራዊ ማዓርጉ ማግኘት አለበት፣ ሀይማኖቱ፣ ብሄሩና የፖለቲካ እምነቱ ግምት ዉስጥ ሳይገባ።) መከላከያ ሰራዊታችን (በተለይ ወታደራዊ መኮነኖች) የብሄር ወይ ክልል ተዋፅዖ የለውም። የፓርቲ ተዋፅዖ ነው ያለው።

 

መኮነናዊ ማዓርግ የሚሰጠው በብሄር ሳይሆን በፖለቲካ ነው (የህወሓት፣ የብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደኢህዴን ምናምን እየተባለ)። ማንኛውም ትግርኛ ተናጋሪ ወታደራዊ ማዓርግ የሚሰጠው ይመስላችኋል? የህወሓት ደጋፊ (በውስጥ አባል) ካልሆነ በቀር? ወታደራዊ ማዓርግ የሚሰጠው በፖለቲካ አመለካከቱ ነው። እንኳን መኮነኖች የጉምሩክና ገቢዎች ሰራተኞችም በፓርቲ ተዋፅዖ የተዋቀሩ ናቸው። በዚሁ መሰረት የህወሓት ወታደራዊ መኮነኖች ሲቀነሱ፣ የብአዴን፣ ኦህዴድና ደኢህዴን መኮነኖች ሲጨምሩ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ የህወሓትን ዓቅም በሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች እየተዋጠ መሄዱ የሚያሳይ ነው። የህወሓት የበላይነት እያበቃ መሆኑ ምስክር ነው። ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው። አሁን በሌሎች ክልሎች ይሰልሉ የነብሩ ህወሓቶች ተባረው በትግራይ መቐለ ከተማ ተሰባስበዋል። ይህን ሁሉ የሚያሳየው የህወሓትን መዳከም ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን እንቀጥላለን!!!

 

 

መከላከያ ሰራዊታችን ከአንድ ፓርቲ አገልጋይነት ወደ ሀገር አገልጋይነት (ሀገራዊ ሰራዊት) እናሸጋግረዋለን። ሰራዊቱ አይፈርስም ግን የፓርቲ ሳይሆን የሀገር (የመንግስት) ይሆናል።

 

 

7 Comments

  1. We have clear and concise tangible info that the so called Ethiopian army is simply a tigrian army. Stop denying it. that is the fact

  2. Megnot new zena dedeb neh min endemtsif enkuan atakim arstuna tsehufu beftsum aygenagnim.kebatari dedeb tegre enkuan hewohat tegre hulu bitefa yeethiopia hizb des new yemilen demo bekerbu yehonal.

  3. We don’t trust you guys, you, Siye, Gebru, blablabla. You got no reason to fight TPLF. No reason, you got land from Amhara(though Amhara will come for it soon), Afar, everywhere neighbouring you though your effort failed to get a piece from Eritrea. Are you kidding you expect us to believe you? Are you serious. You talk about Assab, you know why you set that agenda? Just to keep Ethiopians’ mind away from its land in Ethiopia taken by you from Bandaland(Tigray). We are coming back, you will see Wollo, Gondar and Afar leaving away from you, the Eritreans have already gone though you sacrificed the poor Ethiopians who knows little about your war with Eritrea. Every opposition should get itself clear from any politician from Bandaland who serve the interest of enemies.

  4. Abraha is fighting for equality, but some of you who wrote against him here are most probably supporter of woyane. Like: Nesanet, Belachew I am sure that you both are woyane cadres.

  5. woyane adegalai biwedik woyanen lemadan kilash tatikew kefit mesmer kemiselefut yemejemeiyaw anteneh like ende amare aregawi enam wdaja endih ainet terete teret le 4tegn kifil temariwoch kalhone woyanan
    leminawukew aiseram

Comments are closed.

Share