April 19, 2014
3 mins read

በሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ የትንሣኤ ቅዳሴ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ለሰላምና ለአንድነት የቆሙ ምዕመናን ገለጹ

ቅዳሜ ኤፕሪል 19 ቀን 2014 የትንሣኤ ቅዳሴ በዓል ከምሽቱ 6 ሰዓት ጀምሮ በሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን እንደሚደረግ ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙ ምዕመናን ገለጹ። ምእመናኑ ለዘ-ሐበሻ በላኩት መግለጫ መሠረት አንዳንድ ከወያኔ መንግስት ጋር ያደሩና በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ የገቡ ፖለቲከኛ ግለሰቦች በደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ የቅዳሴ ስነስርዓት እንደማይኖርና ቅዳሴ በሌላ ቦታ እንደሚደረግ በቴክስት መልዕክትና በበራሪ ወረቀት የሚገልጹት ከእውነት የራቀ ነው።

የቤተከርሲቲያኑ ጉዳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ እስከሚወሰንና በፍርድ ቤትም የማንም ፓትሪያርክ ስም በጠቅላላ ጉባኤ እስከሚወሰን ድረስ እንዳይጠራና ማንም እንዳይጋበዝ በጊዜያዊነት አግዶ እያለ በዚህ መሃል አንዳንድ የቤተክርስቲያኒቱ ካህናት “የአቡነ ማቲያስን ስም ካልጠራን አንቀድስም” በሚል ለቤተክርስቲያኑ ደብዳቤ መጻፋቸውን የሚገልጹት አስተያየት ሰጪዎች ‘በትንሣኤ በዓል ቤተክርስቲያኑን ጥለው መሄዳቸው ለሰላም እና ለአንድነት አለመቆማቸውን ያሳያል፤ እንዲሁም ቤተክርስቲያኑን ለመበተን ቆርጠው መነሳታቸውን በግልጽ የሚያሳይ ነው ሲሉ ይተቻሉ።

ምንም እንኳ ምዕመናኑን ለማሳሳት የትንሣኤ ቅዳሴ ከደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ውጭ ይደረጋል በሚል እየተነገረ ያለው ነገር ደብረሰላምን ለመከፋፈል የሚደረግ ሴራ እንደሆነ ምእመናኑ እንዲገነዘብ ያሳሰቡት ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙት ምዕመናን ሕዝቡ እየተነዛ ያለውን በደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ.ክ ቅዳሴ አይኖርም አሉባልታ ወደኋላ በመተው በቤተክርስቲያኑ በሃይማኖት አባቶች ስርዓተ ቅዳሴ ስለሚደረግ በደመቀ ሁኔታ የትንሣኤን በዓል እንዲያከበር ጥሪ ቀርቧል።

የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ አድራሻ 4401 Minnehaha Ave. S Minneapolis, MN 55406 USA እንደሆነ ይታወቃል።

ለጊዜው ወደ አባ ሃይለሚካኤል ስልክ ደውለን የርሳቸውን ሃሳብ ለማካተት ያደረግነው ጥረት ባይሳካም ከሁሉም ወገን ተጨማሪ መረጃዎች ካሉ ይዘን ለመቅረብ እንሞክራለን።

2 Comments

  1. I say may the lord grant aba h/micheal inner repentance for last Sunday’s action. remember it was palm Sunday (HOSAENA) he left the whole congregation in limbo
    god is good we had merigeta to resume the service, his plan was to shut us up on that special day. (sew yasebal egziabher yfsimal) please back off merigeta we know who is divisive in our church it is proven in so money occasion, if you are a true Christian think about others feeling too not only about your self please do not say blind folded we know who is blind folded. MAY GOD GIVE US HONESTY .

  2. I am very sad and my saddest day in my orthodox life, the priest live the church unfashionable in palm sunday’s living the service for his selfish wish to have a piece of land back home taking money from wiyanes cadres. Thanks good we have MEREGATE GATAHUN and wonderful Daikon they savethere people standing with us with there brave and courage’s work. MEREGATE and his followers ready to face any conditions with out showing no fear. Our Easter ceremonies were wonderful he perform like always was supper for the first time we all have a good time. Those people which live our church to the park stop stealing our church property, because one-way-the other you will return it before or after May 11/2014. One more time those priest and daikon which leave our church please don’t came back we don’t need you we have MEREGATA a wonderful priest, teacher and and a wonderful Daikon. Where ever you guys are good luck we tired-of you. Bye.

Comments are closed.

Previous Story

የኢሕአዴግ የደህንነት ሚ/ር አቶ ጌታቸው አሰፋ በአጭር ጊዜ ቢሊየነር ሆነዋል * ዘረፋው ቀጥሏል

Next Story

ይድረስ ለሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ቦርድ አባላት – ”ለእውነት አብረን እንቁም”

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop