May 5, 2023
6 mins read

አብይ አህመድ በይፋ በአማራ ህዝብ ላይ የከፈተውን ጦርነት በመቃወም በጎንደር የቀጠለው ህዝባዊ እምቢተኝነት

1) ጦርነቱ
344955135 6008300689280823 1219008105930953850 n 1 1
ጎንደር

ላለፉት ስድስት ቀናት በአማራ ክልል የሚደረገው ውጊያ የሌላ ትልቅ ጦርነት እና አካል መጀመሪያ ነው። ጦርነቱ የተከፈተው የአማራ ክልል መዋቅርን ሙሉ በመሉ ለመቆጣጠር የተደረገው ሙከራ መክሸፍ ተከትሎ ነው። የአብይ አስተዳደር ከወራት በፊት የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን የእኔ በሚላቸው ሰዎች ቁጥጥር ውስጥ አድርጎ ለመቆጣጠር [domestication] ያደረገው ሙከራ አባ ሳዊሮስ የፈለጉትን ቦታ በማጣታቸው በጉልበት ቤተ ክርስትያኗን ለማንበርከክ ሞክሯል። የኦፕሬሽኑ ስትራቴጂ ሲከሽፍ ወደ ከፍተኛ የሀይል እርምጃ የተኬደበት ስሌት የሀይል እርምጃው በሚፈጥረው ሽብር ላይ የተመሠረተ ነበር። ሆኖም ሽብሩ የበለጠ ለተቃውሞ መነሳሳትን በመፍጠሩ ምክንያት አላማው በተፈለገው መልኩ ሳይሳካ ቀርቷል።

በአማራ ክልልም በተመሳሳይ መልኩ በልል የሀይል አጠቃቀም የደህንነት ተቋሙን እንደ ዋና መሳሪያ ይዞ የመዋቅር ቁጥጥር ለማድረግ ተሰርቷል። ኦፕሬሽኑ [ sabotage and subversion tactics ] በመጠቀም እንዲሁም ልዩ ወዳጅ እና የልዩ ጠላት ዳይኮቶሚ በመፍጠር የታቀደ የፖለቲካል ኮንትሮል ነበር። በዚህ ስትራቴጂ አብይ ትልቅ ድል አግኝቶ የክልሉን ኦውቶኖሚ መሸርሸር እና በከፊል ገባሪ አስተዳደር ለመፍጠር ችሎ ነበር።
ሆኖም በዚህ ሂደት ውስጥ ባልተጠበቀ መልኩ ከኤርትራ ጋር በፍጥነት ያደገው ተቃርኖ የአብይን የቁጥጥር ፍላጎት በከፍተኛ መጠን አሳድጎታል። ይህን ተከትሎ መዋቅሩ ላይ ፍጹማዊ ቁጥጥር [Absolute control] ለመያዝ ተንቀሳቅሷል። የቁጥጥሩ ዋነኛ አላማ በመጀመሪያ የአማራን ፖለቲካ እና አቅሞቹን ማኮላሸት እና ፍጹም ገባሪ ማድረግ ሲሆን በመቀጠል ደግሞ ክልሉን የውክልና ጦርነት ባለቤት አድርጎ የውጊያ መነሻ ሜዳ [staging area] ማድረግ ያለመ ነው።
ይህን አላማ ለማሳካት የአማራ ክልል አስተዳደርን የምስለኔ ሚና ያለው [Vasal state] እንዲሆን ሞክሯል። ሆኖም ይህ ውሳኔ የውስጥ ተቃርኖ ከመፍጠርም ባሻገር ለውሳኔው መተግበር ልዩ ሀይሉን እና ፋኖን በጠላትነት መበየኑ አደገኛ መዘዝ ነበረው። የክልሉን አስተዳደር በፖለቲካዊ እና የደህንነት መሳሪያዎች ለመቆጣጠር የተደረገው ሙከራ ባለመሳካቱ ከፍተኛ ሀይል ተጠቅሞ ለማንበርከክ እየሞከረ ይገኛል። [ Due to a failure of the original plan of grand cooption, a swift transition from administering soft power toward hard power measures, using overwhelming military force, has undertaken.] እንደ ከዚህ በፊቱ ከፍተኛ ሀይል ተጠቅሞ አሸብሮ የማስገበሩ አላማ እጅግ ወደ ተባባሰ ተራዛሚ ግጭት እና ተደራራቢ ተቃርኖ እያደገ ይገኛል።
ሆኖም ይህ ውጊያ ከላይ እንደተጠቀሰው አማራ ክልል ተጀምሮ እዚያው የሚጠናቀቅ ሳይሆን ሌላ ታሳቢ ኮንቨንሽናል ውጊያ ማድረግን ታሳቢ አድርጓል።
2) ለጦርነቱ ምላሻችን
የአማራ ህዝብ በዚህ ወቅት ተገዶ በገባበት ጦርነት መንትያ አላማ አንግቦ የሚታገል ይሆናል። አንድም የተጋረጠበትን ህልውና አደጋ መቀልበስ ሲሆን ሁለት ደግሞ የፖለቲካ አቅሙን አደርጅቶ የህዝቡን ፍላጎት በሚገባው ልክ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተገቢውን ሚና እንዲወጣ ለማስቻል ነው።
በዚህ አላማ እና ፍላጎት ልክ ለመንቀሳቀስ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮችን ባማከለ መልኩ ምክክሮች እና አደረጃጀቶች መፍጠር ይገባል። መፍጠን አለብን። ጊዜ የለንም ብቻ ሳይሆን ጊዜ ከእኛ ጋር ሆኖ አያውቅም በሚል መንፈስ በፍጥነት መስራት አለብን።
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ከፋሽሰት ኢጣሊያ ጀምሮ በተከታታይ በመጡ ፋሽቶች በተከፈተው ጦርነት የተጋረጠብንን አደጋ መቀልበስ እና የመጨረሻውን ጦርነት ለማድረግ \
ዝግጁ መሆን አለብን። ከዚህ በኋላ የምንጠብቀው መዳንም ሆነ የተሻለ ጊዜ የለም።
አዎ …. ጊዜው አሁን ነው !
ድል ለአማራ !
ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር
345422208 626514482866075 8368365506613126796 n
ጎንደር
345058918 259899726603928 5009106995534080251 n
ጎንደር
345055636 1227581407902343 3760398982144833805 n
ጎንደር
344938723 990349128628667 7144196975999732430 n
ጎንደር
abiy geday
#image_title

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop