የአብይ አህመድ ሀገርን የማፍረስ እንቅስቃሴ በፕሮቴስታንት ሃይማኖት በኩል

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሀገር የማፍረስ እንቅስቃሴውን በፕሮቴስታንት በኩል አውጇል፡፡ ኢትዮጵያዊያንን በሃይማኖት በኩል ለማጨፋጨፍ በሚሊነየም አዳራሽ በበጋሻው ደሳለኝ አማካኝነት የጥፋትን አዋጅ አሳውጇል፡፡ የዝግጅቱ አላማ ሙሉ በሙሉ ፖለቲካዊ ነው፡፡

በጋሻው ደሳለኝ የዝግጅቱን አላማ ሲገልጽ፡-

  1. ለብሔራዊ ንስሀ እና ለአማኞች አንድነት ጥርጊያውን ማዘጋጀት ነው (3x)፡፡
  2. ንጉሳችንን ክርስቶስን በአደባባይ ማክበር ነው (1x)፡፡
  3. ለሚመጣው ሀገራዊ ጉብኝት እና መነቃቃት ቤተ ክርስቲያንን መቀስቀስ እና ማንቃት ነው (3x)::

አብይ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ እና ከፖለቲከኞች የሚደርስበትን ጫና ለመገታተር እና የፕሮቴስታንት ምዕመናንን ከጎኑ ለማሰለፍ አዋጅ አስነግሯል፡፡ የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ተከታዮች ከጎኑ እንዲሰለፉ ግልጽ ጥሪ አቅርቧል ተግባራዊ እንቅስቃሴም ጀምሯል፡፡ እኔ በሃይማኖት ስም የኢትዮጵያዊያን ደም በከንቱ እንዳይፈስ ያሳስበኛል፡፡ ይህንን እንቅስቃሴ ልናጋልጠው እና ልናስቆመው ይገባል፡፡

ኃላፊነቱን መወጣት ሲያቅተው ሄዶ ከሃይማኖት ጋር መለጠፉን ማቆም ይኖርበታል፡፡ ይህ ሀገርን የሚያፈርስ እና በኢትዮጵያዊያን ላይ ጥፋት የሚያደርስ አደገኛ እንቅስቃሴ ነው፡፡ይበልጥ ኢትዮጵያን የሚያፈርስ እንቅስቃሴ ላይ እየተሳተፈ ነው፡፡ በቃህ ሊባል ይገባል፡፡ ቀድመን ልናስቆመው ይገባል፡፡

 

አብይ ዛሬውኑ ስልጣን ሊለቅ ይገባል!!!

ሙሉ በሙሉ ኃላፊነቱን የማይወጣ ሆኗል!! ይልቁንም ስልጣኑን አግባብ ባልሆነ መንገድ እየተጠቀመበት ነው!!

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከ3 ሚሊዮን ዲያስፖራ በቀን አንድ ዶላር እንያዲዋጣ በዶ/ር አብይ ከየተጠቀው ውስጥ እስካሁን ያዋጣው 2800 ሰዎች ብቻ መሆኑ ተገለጸ

5 Comments

  1. የዛሬ 7 ዓመት ኢየሱስ በራዕይ በመስቀል ላይ ሆኖ ያየኛል። እኔን የጠራኝ ኢየሱስ ነው ….በጋሻው ደሳለኝ።
    ***
    በትልቅ ውሸት የተጀመረ የቅጥፈት ስብከት
    **
    በጋሻው ደሳለኝ በሚሊኒዬም አዳራሽ ፕሮግራሙ ” እኔን የጠራኝ(ፕሮቴስታንት የሆንኩት) ኢየሱስ ነው።በራዕይ መስቀል ላይ ተቸንክሮ ዝም ብሎ ያየኛል።የኢየሱስ መመልከት እንደበፊቱ ኦርቶዶክስ ቤት እንድቀጥል አላደረገኝም””””
    …..ሲል በእንባ ጭምር ሆኖ ሲያነባ ተመለከትኩ።አዞ እራሱ ይህን የማንባት ዘዴ አያውቀውም።
    ይህ ድልብ የውሸት ድራማ ነበር። ከውሸትም ከፍ ብሎ የሚታይ ውሸትን የማስቀጠል ልዩ ፍቅር የታዬበት ታላቅ ውሸት
    እንዴት በለኛ ባሻዬ?
    አቶ በጋሻው ደሳለኝ እና ትዝታው ሳመኤል የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ገደማ ዘማሪ ገብረአምላክ ደሳለኝ ለተባለ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ወጣት ዘማሪ የግጥም እና ዜማ ከሰሩ አገልጋዮች መሃል አንዱ ነበር።
    የዝማሬውም ርዕስ “ካልባረከኝ አለቅህም “ይባላል። በእርግጠኝነት ብዙዎቻችን ይህን ዝማሬ ዘምረነዋል።
    በእዚህ ዝማሬ ውስጥ በጋሻው ደሳለኝ እና ትዝታው ሳሙኤል ግጥም ሰጪ ነበሩ።
    የሰጡት ግጥም የማን ቢሆን ጥሩ ነው ትላለህ። ሙሉ በሙሉ ኮፒ ፔስት የተደረገ አንድም የቃል ጭማሪም ሆና አንድም ቅነሳ የሌለበት የፕሮቴስታንት ዘማሪ የሆነው ዶ/ር ደረጄ ከበደ ነበር።
    ለካ እነርሱ እሁድ እሁድ አውደ ምህረት እየቆሙ እያስተማሩ ማታ ማታ የፕሮቴስታንት ዝማሬ እና ስብከት ነበር የሚሸከሽኩት ።
    ወዳጄ በጋሻው ደሳለኝ ….ፕሮቴስታንት የነበረው የዛሬ ሰባት ዓመት ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሆኖ ተሰቅሎ በራዕይ ተመልክቻለውኝ በሚል ግዙፍ ውሸት ሳይሆን ድሮሮሮ በመቅደስ ውስጥም ሳለ ነበር።
    ስለዚህ ለበጋሻው ደሳለኝ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ሰው ለመሆኑ ራዕይ፣ የኢየሱስ መስቀል ምናምን ተብለው በሚሊኒዬም አዳራሽ በእንባ ጭምር ታጅበው የተነገሩ ድራማዎች ሳይሆን …..ከዘጠኝ ዓመት በፊት የነበረው ፕሮቴስታንት የመውደድ ፎንቃው ነው።
    የራዕይ ድራማህን ማስቀጠል መብትህ ነው ። ሰውን በውሸት መሸወድ ግን አይቻልም ባሻዬ።
    በውሸት የተጀመረ ስብከት መጨረሻው ምን እንደሆነ የሴጣን እና የሄዋንን የበለስ ላይ ስብከት መመልከት በቂ ነው።
    Kune Demelash kassaye -Arba Minch

    • አይ አንተ የሀይማኖት ሸኔ የሆንክ ሰው እንደው ምን ይሻልሀል። ጉድጓዱን አርቀህ ባትቆፍር ጥሩ ነው መውደቂያህ የት እንደሆነ አይታወቅምና። አክራሪ ፅንፈኛ!

    • አንተ መዝሙሩ የዶክተር ደረጀ መሆኑን በምን አወቅህ?

  2. ቀልደኞች። ያበደ ሰዉ ስራ አላየንበትም። ሊያሳብዱትና ስልጣኑን በገዛ ፈቃዱ እንዲለቅ የዕብድ ሥራ የሰሩት ግን ራሳቸዉ አብደዉ አይተናል። በዐይናችን የምናየዉን እንናገራለን። ዉሸት ተከምሮ ኪሊማንጄሮን ቢያክል ቅንጣት እዉነት እንደ ዱቄት ትበትነዋለች። ዛሬ እሱን አብዷል የሚሉ ነገ በነፍስ ወከፍ እያንዳንዱን ማበዳቸውን ሁሉም ያየዋል። ሰዉ አጭደዉ ቢከምሩ፥ ጤፉን በፈረንጆች ብር ገዝተዉ ከገበያ ቢያጠፉ፥ ስንዴዉን ገዝተዉ ቢደብቁ አልሆን ሲላቸው ምኞታቸዉን ዜና አድርገዉ የሚያሰሙን ብዙዎች ናቸዉ።

  3. You wish it, Dr. Abiy is the best PM the country ever had. He will finish what he planed for the next 10 years. You are the one who tries to fuel issues here and there. Shamledd

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share