March 3, 2023
5 mins read

ከጠላት ዋሻ ውስጥ ላደገ ወሮበላ ውሻ ፍርፋሪህን ካሳደግኸውና አጥርህን ከሚጠብቀው ውሻህ ጋር እንዲጋራ አትፍቀድ

Abiy stiupid
ከጠላት ዋሻ ውስጥ የያደገ ወሮበላ ውሻ

በመጀመሪያ እንኳን ለ127ኛው የአድዋ የድል በዓል አደረሰን አደረሳችሁ ። አድዋን ስናከብር ጀግኖች መሪዎች ከሌሉ ጀግና ህዝብ ጀግነቱን የሚያሳይ ሥራ መሥራት ብዙ መሰዋእትነት እና ዘመን እንደሚወሰድ እያሰብን መሆን አለበት። ለዚህም ነው የአድዋ ድል እንዲጨበጥ ያደረጉ ንጉስ ነገስት ዳግማዊ አጤ ምኒልክን እና ንግስተ ነገስቻት እቴጌ ጣይቱ ብጡልን በየአመቱ መዘንጋት የለባቸውም የምንለው ።

ወደ እርሱ ስመለስ ግን ዛሬ የባንዳ ልጆችና ማደጎዎች የአብይ አህመድ ኦሮሙማ እና ወያኔ የነ አጤ ምኒልክን ሀውልት ማየት የሚጠሉት እና የሚያስበረግግ መስቀል የሆነባቸው ከቀደመው የባንዳነት ውርሳቸውና አስተዳደጋቸው የመነጨ ነው።

ከጠላት ዋሻ ውስጥ ላደገ ውሻ የትግል መሪነት ወንበር ብቻ ሳይሆን ፍርፋሪ ህን እንጓ ካሳደጋቸውና አጥርህን ከሚጠብቀው ውሻህ ጋር እንዲጋራ አትፍቀድ።

ሹምባሽ በአርበኛ ጓዳ ውስጥ ምን ይሰራል ?

ደሳለኝ ጫኔን ጨምሮ አብዛኛው የዚህ የአብን አጭበርባሪ ቡድን ታሪክ ለማታውቁ ከ2010 በፊት ወያኔን የሚቃወሙ ሰዎችን ይሰልል የነበረ ነው። በዐማራ እና/ወይም ኦርቶዶክስ ላይ ግፍ ሲገዝፍ የት ነበሩ ብሎ የሚጠይቅ የለም ሾርት ሚሞሪ ናቸው ብለው ያስባሉ ልክ እንደ ሿሚዎቻቸው እና ጌቶቻቸው ። ያኔ የብአዴን-ወያኔ ቀኝ እጅ የነበሩ ህዝባችን ማሸነፉን ሲረዱ ተስፈንጥረው ከህዝብ ተቀላቅለው ዐማራውን ለጭፍጨፋው አዘጋጁ ት።

ተስፈንጥረው ዐማራው ሊያቋቁማቸው የጀመራቸውን እንደ አስራት የመሳሰሉ የሚዲያና መሰል ተቋማት አፈራርሰው ወጀ አሳደጋቸው ጓዳ ገቡ።

በነገራችን ላይ እኔም እራሴ አባል የነበርኩበት በአቶ ተክሌ የሻው የሚመራው የዐማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ፖርቲ አብሮ ለመስራት እና የመጣብንን አደጋ ህዝባችንን አሰባስበን እንታገል በማለት አነጋግሮ የፖለቲካ ሰነዶችን ተቀበለው ከተመለከቱ በኋላ ሀሳቦችን ከዘረፉ በኋላ ብአዴን በዐማራ ህዝብ ላይ ከሚያደርገው ማጣጣል በላይ አጣጥለው ነው የመለሷቸው።

ይህ አሳፋሪ ስብስብ የሠራውን የዐህኢአ ወገኖቼ ሊናገሩት ያልፈቀዱት ለዐማራው ትግል ሲሉ ይሆናል ። እኔም የእነሱን ለትግሉ መቆርቆር ተመልቼ ዝም ብየ ነበረ።

አሁን በቃኝ። የዐማራ ትግል ልክ የአድዋው አይነት የአንድ ጀምበር ፍልሚያ ብቻ የሚጠይቅ እንጅ ለአመታት ህዝብ እየታረደ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት ወደኋላ የሚጓዘው በነዚህ አይነት ከተፈለፈሉበት ቅርፊት ጋር እንዲያታግሉንና እንዲታገሉልን በጊዜያችንን እና ገንዘባችንን ስለምናባክን ነው።

ተራው የአብን እና የብአዴን አባላት እነዚህ ሁለቱን ታጥበው የማይጠሩ ሽንፍላዎች አሽቀንጥሮ በመጣል ከመሪዬ እስክንድር ነጋና ጀግኖች የዐማራ ፋኖዎች ጋር አንድ የትግል ተቋምእንዲኖረን እንዲሰሩ እና ይህንን እንዲያደርጉ ጥሪየን አቀርባለሁ ።

ዛሬ ህዝብ ልክ በፋሸሸት እንደተወረርንበት ዘመን አምርሮ መነሳት ሲጀመር ለምን መጡ የሚለው ጥያቄ ላይ ሰመጣ፥

ዛሬ በመሪዬ በአርበኛው እስክንድር ነጋ እና በዐማራ ወጣቶች መናበብ በገሃድ እና በተግባር ሲመለከቱ ዘልለው ሊሰፍሩብንና ትግላችንን ሊያቀጭጬ ተከስተዋል ።

አሁንም ሊያታልሉህ ይችሉ ይሆን?

አይመስለኝም ።

ኑርልኝ- የካቲት 23 2015 ዓ.ም

 

https://zehabesha.com/open-letter-to-the-norwegian-nobel-committee-3/

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop