March 2, 2023
2 mins read

የአድዋን የድል ቀን ወደ ውርደት ቀን የቀየሩትን የመንግስት ባላስልጣናት ልናወግዛቸው ይገባል

334204880 572766811246492 4904635407289962123 n 1 1 1 1 1

334204880 572766811246492 4904635407289962123 n 1 1 1 1 1ይህ በአል ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ተሳትፎ በከፍተኛ ድምቀት በምኒሊክ አደባባይ ይከበር ነበር። እኔም አንዱ የህዝብ አካል ሆኜ ተሳትፌበት አውቃለሁ። በዛሬው እለት ግን በምኒሊክና በመስቀል አደባባይ የከተማው ህዝብ ድርሽ እንዳይል ከልክለው፣ በበአሉ የታደሙት የብልጽግና ከፍተኛ ባላስልጣናት፣ ካድሬዎችና ብልጽግና ድህነታቸው የታማኝነት ማሰሪያ ሰንሰለት አድርጎ በጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅቶች ያደራጃቸው ምስኪኖች ብቻ ናቸው። ሌላው ህዝብ ወደ አደባባዮቹ እንዳይደርስ በወታደር፣ በፌደራል ፖሊስና በከተማው ፖሊስ እንደ ከብት ከመንገድ እየተነዳ እንዲወጣ ተድርጓል።

በአንዳንድ ቦታዎች በድብደባ ጉዳት የደረሰባቸው እንዳሉ መረጃው ደርሶኛል። ሁኔታውን ለተመለክተ ቀኑ የበአልና የደስታ ሳይሆን ከተማው በጠላት ተወሮ የሃዘን ጥላ ያጠላበት ቀን ይምስል ነበር። ይህ በወሬ ሳይሆን በአካል ወደ መስቀል አደባባይ ከጓደኞቼ ጋር ለመሄድ ሞክሬ ከደረሰብኝ ተነስቼ ነው የምጽፈው። እንኳን ለዚህ ቀን አበቃህ የምትሉ ምጸተኞች እንዳላችሁ አውቃለሁ። በምጸታችሁ አላዝንም። የማዝነው ከታሪክ መማር ለተሳናቸው እብሪተኛ የሃገሪቱኛ ገዥዎች ነው።

V Day turned into a day of ignominy. Residents of Addis were denied the right to celebrate the V of Adwa at any of the city’s public Squares.Only PP affiliates, officials and cadres were allowed to get into Meskel Square.Menelik Sq was also off the limit to revellers.I was there

Andargachew Tsige

3 Comments

  1. አይ ጋዜጠኛ ይህንን መርዘኛ ስለ አድዋ ጠየቅኸው የጻፈውን መጽሃፍ ስላላነበብከው አልፈርድብህም፡፡ ብርሃኑንም ብታገኝ ትጠይቀው ነበር በል እንግዲህ ሽመልስ አብዲሳንም ቀጀላ መርዳሳንም አብረህ ጠይቃቸው፡፡ ክክክክክክ

  2. ዓይንህ ምኒልክ ላይ አየሁት ሲቀላ
    ጌታህን አወቅኩት በመላ በመላ።
    ዓይንህ ደም ሲለብስ በቴጌ ጣይቱ
    ጌታህን አወቅኩት እስከ ምንዝላቱ።

  3. ሽመልስ አብዲሳ ኦሮምያን ማስተዳደር ስላልቻለ ወለጋ ከቁጥጥሩ ውጭ ስለሆን ከቦታው ይባረር ይታሰር ተጠያቂ ይሁን

Leave a Reply

Your email address will not be published.

331313711 237496782045209 6212273173327933092 n 1
Previous Story

የአድዋ ድል የጋራ ስኬታችን፤ የአንድነታችን ተምሳሌት ነው!

56666666 1 1
Next Story

የአድዋ በዓል እንዲ ተከበረ ዛሬ 23/6/2015

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop