March 2, 2023
5 mins read

የአድዋ ድል የጋራ ስኬታችን፤ የአንድነታችን ተምሳሌት ነው!

331313711 237496782045209 6212273173327933092 n 1

“ኢትዮጵያ ባለ ብዙ ባህል፣ ታሪክና ቅርስ ባለቤት ናት። ጥሩዎቹን እንንከባከባቸዋለን፤ መጥፎዎቹን እንማርባቸዋለን”  የኢዜማ ፕሮግራም

ኢትዮጵያ በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች የተጋረጡባትን ፈተናዎች አክሽፋ ህልውናዋን ያስጠበቀችው በልጆቿ ጠንካራ አንድነት ነው፡፡ በተለያየ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአራቱም አቅጣጫ በኢትዮጵያዊነቱ ተሰባስቦ የጋራ ቤቱ የሆነችውን ኢትዮጵያን ከህልውና አደጋ አትርፏል፡፡ የመጣውን ሀገራዊ አደጋ በአንድነት ኾኖ መክቷል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ህልውና በጋራ ጥረት እንጂ ለእኔና የእኔ ብቻ በሚል ከፋፋይ አስተሳሰብ እንደማይጠበቅ በተደጋጋሚ ትምህርት ሰጥቶ አልፏል፡፡

በተለይ ዛሬ የምናከብረውን የአድዋ ድል ዞር ብለን ስናይ በጉልህ የምናየው የአፄ ምኒልክ አመራር ጥበብን፣ የእትጌ ጣይቱ ወኔና አስተዋይነትን፣ የመሳፍንት እና መኳንንቱ ሀገርን ከምንም በፊት የማስቀደም መርህን፣ የመላው ህዝብ በኩራት በጋራ መቆምን እና ዛሬ በስም የማናውቃቸው አያሌ ጀግኖችን አኩሪ ተጋድሎ ነው፡፡

በአጠቃላይ በአልደፈርም ባይነት የተከፈለ መስዋትነትን፣ በሕብረት በመቆም የተከበረ ማንነትን፣ ልዩነትና አለመግባባትን ለሚገባው ቦታና ሰዓት አቆይቶ ከሀገር ሉዓላዊነት ጎን መቆምን፣ ከምንም በላይ ደግሞ የሰው ልጅ ሁሉ እኩል መሆንን በተጨባጭ ያሳየ አፍሪካን ያነቃቃ የቀደምት አባቶቻችን አኩሪ ገድል መኾኑን ነው፡፡

የድል በዓሉን ስናከብር ቀደምት አባቶቻችን የተዋደቁለትን ሀሳብ በሚገባ ልንገነዘበው ያስፈልጋል፡፡ አባቶቻችን መስዋዕትነት የከፈሉት ለኢትዮጵያዊነት፤ ለሀገራዊ አንድነት፤ ለጋራ ቤታችን ህልውና፤ ለክብርና ማንነታችን መጠበቅ፤ እንዲሁም ለነፃነታችን ነው፡፡ የአድዋ ድል ወራሾች መኾን የምንችለው የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት፤ ሉዓላዊነት፤ ክብር፤ ህልውና እና ነፃነት ማስጠበቅ ስንችል ብቻ ነው፡፡

የአድዋ ድል አንድምታ መንፈሳችንን ሊያነቃው፤ አንድነታችንን ሊያጠብቀው፤ ክብራችንንም ሊያስጠብቀው ይገባል፡፡ የአድዋ ድል የአንድ ቀን ክብረ በዓል ብቻ መኾኑ ቀርቶ፤ ድሉ ያጎነፀፈንን ትሩፋቶች በአግባቡ ልንጠብቃቸው ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነቱ ከተሸረሸረ፤ ነፃነቱ ከተገፈፈ፤ ዴሞክራሲ ከራበው፤ ልማት ከናፈቀው እና ሰላምና ደህንነቱ ካልተጠበቀለት የአድዋ ድል ትርጉም ያጣል፡፡ አያት ቅድመ አያቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ያስረከቡንን ሀገር አጥንት ቆጠራ ላይ መሠረት ባደረገ የዘውግ ፖለቲካ አንድነቷን እየሸረሸሩ የአድዋ ድልን በዓመት አንድ ጊዜ ማክበር ይህ የተከፈለውን መስዋዕትንት ገደል መክተት ነው፡፡

ፓርቲያችን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአድዋ ድል ያስገኘለትን ትሩፋቶች ይጠቀምባቸው ዘንድ የዜግነት ፖለቲካ፤ ማኅበራዊ ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፌደራሊዝም እውን መኾን እንዳለባቸው ያምናል፡፡ የዘር ፖለቲካ ባለበት፤ የሀብት ክፍፍል ሚዛን ባልተጠበቀበት እንዲሁም ሕዝብ በትክክል ዴሞክራሲን ተጎናፅፎ ራሱን በራሱ ማስተዳደር በማይችልበት ኹኔታ በአድዋ ድል የተገኘው ነፃነት፤ ክብር፤ ሉዓላዊነት እና አንድነት ለዛሬው ትውልድ የማይጨበጥ ተስፋ ኾኖ እንደሚቀር ማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

ዘላለማዊ ክብር ለአድዋ ጀግኖች!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

የካቲት 23፣2015 ዓ.ም

#የዜግነት_ፖለቲካ

#ማኅበራዊ_ፍትህ

#ኢዜማ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop