December 17, 2022
5 mins read

የግብጹ ባንዲራና የጥላቻው መዝሙር (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

rrrrrrrየኦሮሞ ፖለቲከኞች የኦሮሞ ሕዝብ ዲሞክራሲ አላገኘም በሚለው ይስማማሉ። በዲሞክራሲያዊ መብት የመጠቀም እድል ካላገኘ ዛሬ የተጫነበትን የግብጽ ባንዲራም አልመረጠም ማለት ነው። የጥላቻውንም መዝሙር አልጻፈም፣ አላጻፈም፣ በዲሞክራሲያዊ አግባብ ተስማምቶ አላጸደቀውም ማለት ነው።

ራሱ የኦሮሞ ሕዝብ የኔ ነው ያላለውን ሰንደቅ ዓላማ እና የጥላቻ ድርሰት ሌሎች እንዲያውለበልቡ ማስገደድ ከኦሮሞም ከሌላውም ሕዝብ ፈቃድ ውጭ የሆነ የፋሺስቶች፣ የመልካም ራዕይ አልባዎች፣ የግጭት ነጋዴዎች ተግባር ነው። ይህንን መቃወም ደግሞ በተቃራኒው ለዲሞክራሲ መታገልና እጅግ ፍትሐዊ ተግባር ነው። ባንዲራው የግብጽ ነው። መዝሙሩም የጥላቻ ድርሰት ነው። ይህንን ባእድና አዋራጅ ጭነት መቃወም የአርበኝነት ሥራ ነው።  አጀንዳው ግን በዚህ ወቅት የተመዘዘው በግርግርና በሽፋኑ የክህደቱን ድርድር ለማስረሳት ይበልጥ ደግሞ የወለጋውን የንጹሐን ጭፍጨፋ ለማሳለጥ፣ የአማራን ጄኖሳይድ በክፍተኛ ደረጃ ከሕዝብ ትኩረት ውጭ ለማድረግ በመሆኑ የወንጀል ወንጀልና፣ ከከረፋ ቆማሪ ኅሊና የመነጨ አዳፋ ተግባር ነው።

እኔ በግሌ የኦሮሞ ሕዝብ ሰንደቅ ዓላማዬ ነው ያለውን በፈቃደኝነት ባውለበልብ ግድ የለኝም፣ መዝሙሬ ነው ያለውን ብዘምርም ደስ ይለኛል። ሀገር አፍራሽ፣ የአክራሪ እስልምና አጀንዳ አራማጆች በስውርና ዘመናትን በዘለቀ ማጭበርበርና ደባ የአክራሪ እስልምና አላባ፣ የግብጽ ባንዲራ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ በኦሮሞ ላይ እንደጫኑበት በእጅ አዙር እኔም ላይ ሊጭኑብኝ ቢሞክሩ ግን አልቀበለውም። መዝሙሩንም እህትና ወንድሜ አጥንትና ደሜ የሆኑ የኦሮሞ ልጆች በኢትዮጵያዊና አፍሪካዊ መንፈስ ተቃኝተው ለሕዝባቸው መልካም ራእይ ሰንቀው የደረሱትና ሕዝቡ የተቀበለው ከሆነ በደስታ አሁንም በፈቃደኝነት ብዘምረው ደስታዬ ነው። የአረብና የፈረንጅ ተላላኪዎች ሀገር ለማፍረስ፣ አፍሪካን ለሌላ ዙር ቀኝ ግዛት ለማመቻቸት የወጠኑትን የጥላቻና የበቀል ጥንስስ ድርሰት ልጆቼ እያጠኑ እንዲያድጉ ልፈልግ ቀርቶ ልሰማውም አልፈቅድም።

የኦሮሞ ልጆች ከአብዲሳ እስከ ቀነኒሳ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርገው ያውለበለቡ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር የሚዘምርለትን ነጻነት እውን ያደረጉ ናቸው፤ ዘላለማዊ ክብር ይገባቸዋል። ከዙፋን እስከ ጫካ ያሉት ባንዶች ደግሞ ኢትዮጵያን የሚያዋርዱ፣ መሠረቶቿን የሚንዱ፣ ከባእዳን ጋር የሚሞዳሞዱ ናቸውና እንደሌላው ብሔር ባንዳ ሁሉ ዘላለማዊ ተቃውሞ ይገባቸውል።

ይሁንና ተቃውሞው መጀመሪያ ባንዲራውና መዝሙሩ የኦሮሞ ሕዝብ ባንዲራ እና መዝሙር አለመሆኑን በማጋለጥ ቢጀምር። ሲቀጥል በስናይፐርና በገጀራ ለመፍጀት ዝግጅት ጨርሶ ለተቀመጠው የአቢይ አህመድ ጦር ሕፃናትና ወላጆችን ሲሳይ በማያደርግ መልኩ ቢካሄድ። ሦስተኛም ፍጅትና ግጭት፣ ግድያን ጠንስሶና ጠምቆ የሞቱን ድግስ ከርቀት ለመታዘብ ከሀገር ውጭ የሚጓዘው አቢይ አህመድ እሳትም ከተነሳ አብሮ እንዲበላው ጌቶቹ ጠርተውት ከሄደበት እስኪመለስ ቢጠበቅ።

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop