October 28, 2022
11 mins read

አሪሂቡ አፍሪካ – በስንታየሁ ግርማ አይታገድ

በስንታየሁ ግርማ አይታገድ (0900065962)

ሕይወቴን በቡና ስኒ ለካሁ። – ቲ.ኤስ.ኤል የዘፈነዉ ነዉ፡፤

coffeeበአለም አስደናቂው የ ኢትዮፕያ መለያ የሆነዉ ቡና በዘጠነኛዉ ክፍለ ዘመን በሀገራችን ተገኘ፡፡ከዛም ወደ አረቡ አለም ተሸገረ፡፡በመቀጠል በባሪያ ንግድ እና በቅኝ ገዢወች አማካኝነት በሶስተኛዉ አለም እየተመረተ አወሮጳ እየተላከ የቡና መጠጣት ባህል ተፈጠረ፡፡ቡና የምዕራቡ አለምን ከመጠጥ ሲሰኝነት በማላቀቅ ባለዉለታ ነዉ   ፡፡ለምሳሌ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን በእንግሊዝ መጠጥ ከቁርስ ጋር ሳይቀር እየቀረበ በየአመቱ በአማካኝ እስከ 70 ጋሎኖች ይጠጡ እንደነበረ መረጃወች ያሳያሉ፡፡ይሂንና ቡና መጥቶ እንግሊዝን  ጨዋ እና ነጫ ሀገር አደረጋት፡፡

ከቅርብ አመታት ወዲህ የቡና ባህል በአፍሪካ እያደገ ነው፡፡ ምንም እንኳ አፍሪካ ለአለም ከሚቀርበው 13 በመቶ ብታበረክትም እና የቡና መገኛ አህጉር ብትሆንም ከሌላው ዓለም ጋር ሲወዳደር የአፍሪካውያን ቡና የመጠጣት ባህል የተፈለገውን ያህል አይደለም፡፡ ከኢትዮጵያ በስተቀር፡፡ አፍሪካውያን ከሚያመርቱት ምርት አብዛናውን ለአለም ገበያ የምታቀርብ ፍጆታዋ በጣም ትንሽ ነበር፡፡ አሁን ግን በመጠኑም ቢሆን ሁኔታዎች እየተለወጡ ነው፡፡

የአፍሪካ መንግስታት የሀገር ውስጥ የቡና ፍጆታን እያበረታቱ ነው፡፡ ለምሳሌ ካሜሩን «የቡና ፌስቲቫል» የሚል ሁነት በማዘጋጀት በሁሉም የመንግስት መ/ቤቶች ቡና መጠጣትን እያስተዋወቀች ነው፡፡

በደቡብ አፍሪካም ትኩስና ተሎ የሚደርሱ እና ወደ ቤት ተወስደው ከሚጠቀሙበት መጠጦች ውስጥ በየአመቱ በአማካይ 2.8ቱ የቡና ሱቆች ይሸፍናሉ፡፡ የቡና ኢንዱስትሪውም በአመት በአማካይ በ7.1 በመቶ እያደገ ነው፡፡ የቡና መጠጣት አብዮት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ነው ይላሉ ተንታኞች፡፡

በናይጄሪያም ውስጥ የመካከለኛው ህብረተሰብ ክፍል እያደገ በመምጣቱ እ.ኤ.አ በ2010 እና 2015 በናይጄሪያ ቡና መጠጣት 20 በመቶ እያደገ ነው፡፡

ጥናቶች እንደሚያሳዩት እ.ኤ.አ በ2020 ናይጄሪያውያን 1000 ቶን ቡና ይጠጣሉ ተብሎ ይገመታል፡፡ ይህንን ፍጆታ ደግሞ የናይጄሪያ የቡና ምርት አይሸፍንም፡፡ ይህንን እድል ኢትዮጵያ ልትጠቀምበት ትችላለች፡፡ የአሜሪካ የግብርና ምርት መምሪያ እንደገመተው ኢትዮጵያ በ2022 /2023 በኢትዮጵያ 495ሺህ ሜትሪክ ቶን ቡና በማምረት ሪከርድ የሆነ ምርት በማምረት ኤክስፖርቱም ሪከርድ እንደሚሆን ተንብይዋል፡፡

ከአፍሪካ አብዛኛው የሮብስታ  ቡና አምራች አገራት የሆነችውም ዩጋንዳ የአገር ውስጥ ፍጆታዋን በ20 በመቶ በአማካይ በማሳደግ ኢኮኖሚዋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ትችላለች፡፡ ዩጋንዳም የቡና ባለስልጣን የሀገር ውስጥ ፍጆታን ለማበረታታት ንቅናቄ ጀምሯል፡፡ ይህም በሳምንት ውስጥ 20ሺህ ስኒቡና  በነፃ ማቅረብ ያካትታል፡፡

በጎረቤታችን ኬንያም መካከለኛው ህብረተሰብ እያደገ በመምጣቱ የኬንያውያን ቡና የመጠጣት ባህል ለማሳደግ እና ከሻይ ይልቅ ቡናን እንዲጠጡ ለማበረታታት የቡና ሱቆች በማስፋፋትና በማበረታታት የሸማቹን እምነት ለማሳደግ እየጣረች ነው፡፡

ይሁንና እነዚህ ጥረቶች ሁሉ በቂ ሆነው አልተገኙም፡፡ ከዚህ በመነሳት ከዳበረው የኢትዮጵያ ቡና የመጠጣት ባህል ልምድ ለመውሰድ አፍሪካውያን ከኢትዮጵያ የቡና ባህል ልምድ በመቅሰም እና ወደ ራሳቸው ለመውሰድ በአዲስ አበባ መክረዋል፡፡

ምክንያቱ ደግሞ ኢትዮጵያ የቡና መገኛ አገር ብቻ ሳትሆን ለዘመኑ የዳበረ የቡና ባህል ያላት አገር በመሆኗ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በአማካይ ከምታመርተው የቡና ምርት ከግማሽ በላይ ለአገር ውስጥ ፍጆታ ታውለዋለች፡፡ ይህ ልምድ የኢትዮጵያን ቡና ቀጣይነት ከማረጋገጥ አኳያ መልካም እድል ነው፡፡

በአፍሪካ ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ ቡና የመጠጣት ባህል በተለይም በመጠኑ እየጨመረ ነው፡፡ በከተሞች የቡና ሱቆች እየተስፋፉ ነው፡፡ የመካከለኛው ህብረተሰብ ክፍልም እያደገ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ቡና ኤክስፖረት ማደግ ከፍተኛ እድል ነው፡፡ የአለም የቡና ገበያ ዋጋ ወሰኖች ባደጉ አገሮች ትንሽ ቡና ቆዪዎች እና ድንበር ተሸጋሪ ኮርፖሬሽን ናቸው፡፡ ዋጋውን የሚወስኑት እነሱ በመሆናቸው የአለም አነስተኛ ቡና አብቃይ አርሶ አደሮች ገቢ የምርት ወጪውን እንኳን የሚሸፍን አይደለም፡፡ ይሁንና የኢትዮጵያን ቡና ይህንን ስጋት የመቋቋም እድሎች አሉት፡፡ እነሱም፤

ኢትዮጵያ ብዛት ያላቸው ልዩ ቡና / Speciality Coffeee ባለቤት በመሆኗ 2/3ኛውን ኢትዮጵያ ቡና ልዩ ቡና ተብሎ የመመደብ ብቃት አለው፡፡ ሸማቾች ደግሞ ለልዩ ቡና የተሸለ ክፍያ የመክፈል ልምድ እያዳበሩ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ቡና ከ90 በመቶ በላይ ኦርጋኒክ ተብሎ የሚፈረጅ መሆኑ ከሸማቾች ጤንነት ጋር ተያይዞ ተጨማሪ እየሆነ መምጣቱ እና የተሸለ ክፍያ እያደገ መምጣቱ፤

« ፍትሀዊ ንግድ  »   የሚደረግ ንቅናቄ እያደገ መምጣቱ የቡና ቀጣይነት በአለም በተዛባው የንግድ ስርዓት ምክንያት አነስተኛ ቡና አብቃይ አርሶ አደሮች እየተጎዱ በመሆኑ ፍትሀዊ ንግድ ንቅናቄ አቀንቃኞች አነስተኛ አምራች አ/አደሮች የምርት ወጪያቸውን ለመሸፈን የሚያስችል እና ኑሯቸውን ለመግፋት የሚያስችል ሲስተም እንዲኖር አየጣሩ ነው፡፡ በሸማቹም ተቀባይነት እያገኘ ነው ቡና ጠጪዎች ቡናው የት እንደተመረተ፣ እንዴት እንደተዘጋጀ እና እንደታሸገ በማወቅ የተሻለ ዋጋ ለመክፈል ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡

ከቡና ምርት ጀርባ ያለው አካባቢያዊ፣ ማህበራዊና የአካባቢ ጉዳዮችን ቡና ጠጪዎች በማወቅ የተሻለ ክፍያ ለመክፈል ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡ በድርጊትም እየገለጹ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ ይህንን ስለምታሟላ ለአ/አደሮቻቸው ምርጥ እድል ነው፡፡ ለዚህም ነው የሚቀጥለው አመት የቡና ጣዕም ውድድር ሀገራችን የምታስተናግደው፡፡

የአፍሪካ ኢኮኖሚ ማደግ በአለም ላይ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት አገሮች አብዛኛዎቹ ከአፍሪካ ናቸው፡፡ በአፍሪካ ወጣቱ እና መካከለኛው የህብረተሰብ ክፍል በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ነው፡፡ ቡና መጠጣት በአሁኑ ሰዓት የሞደርናይዜሽንና ስልጣኔ ምልክት እየሆነ ነው፡፡ ጥናቶች እንደሚያሳዩት በቀን ከሁለት ስኒ ቡና በላይ መጠጣት የእድሜ ጣሪያን በ15 አመታት እንደሚጨምር ተረጋግጧል፡፡ እድሜ ጣሪያ ደግሞ ከፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል (HDI) አንዱ ነው፡፡ እያደገ የሚመጣውን የአፍሪካ ቡና ፍጆታ ደግሞ ሊሸፍን የሚችለው የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው የኢትዮጵያ ቡና ምርት ነው፡፡ ስለዚህ ፊታችንን ወደ አፍሪካ ማዞር አለብን፡፡

የኢትዮጵያ ቡና መገኛ አገር በመሆኗ ጥሩ ገጽታ እና መልካም ስም አዳብሯል፡፡ ሸማቾች ደግሞ ከምርቱ በላይ ዋጋ የሚከፍሉት ለመልካም ስም ነው፡፡ስለዚህ የአፍሪካን ወጣት የበለጠ ቡና መጠጣት በማስተዋወቅ ለምሳሌ ከፕርሚርይር ሊግ ከለቦች አንዱን ስፖነሰር በማድረግ ሊሆን ይችላል፡፡

ለምሳሌ ኢትዮጵያ ቡና፣ሲዳማ ቡና ወ.ዘ.ተ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop