August 5, 2022
3 mins read

24 የአልሸባብ አመራሮችን ጨምሮ ከ800 በላይ የቡድኑ ተዋጊዎች ተደመሰሱ

296078933 422557919897991 5110291661004609782 n

296078933 422557919897991 5110291661004609782 n የጸጥታ ኃይሉ በወሰደው እርምጃ እስካሁን ባለው ሂደት 24 የአልሸባብ አመራሮችን ጨምሮ ከ800 በላይ የሽብር ቡድኑ ተዋጊዎች መደምሰሳቸውን ጊዜያዊ የጸጥታ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ፡፡

የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊና የጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስተባባሪ ሜጀር ጄነራል ተስፋዬ አያሌው እና የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል መሃመድ አህመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት ፥ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ከሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ለመግባት ያደረገው ሙከራ በፀጥታ ኃይሉና በሕዝቡ የተቀናጀ እርምጃ ሙሉ በሙሉ ከሽፏል።

ድሽቃን ጨምሮ በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውም ነው የተገለጸው፡፡

ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን ለማተራመስ የሚሹ የውጭ ጠላቶች የውስጥ ባንዳዎችን በመቅጠር ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡

እቅዳቸው እንዳሰቡት አልሳካ ሲላቸው በአሁኑ ወቅት አልሸባብን ከኋላ በመደገፍ ከንቱ ሙከራ ማድረጋቸውንም ነው ያብራሩት፡፡

ይህም ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዎችን ተጠቅማ ለመልማት የጀመረችውን ተስፋ ሰጪ ሥራ ለማደናቀፍ ያለመ ሙከራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም አልሸባብ ኢትዮጵያና ሶማሊያ በሚዋሰኑባቸው አካባቢዎች የተወሰነ ኃይሉን በ16 ተሽከርካሪዎች በመጫንና የተወሰነውን ደግሞ ጨለማን ተገን አድርጎ በእግር ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ በማስገባት ጥቃት ለመፈጸም መሞከሩን ነው የገለጹት፡፡

296388676 422558299897953 1888880498667557029 n 1

ሆኖም የመከላከያ ሰራዊቱ ከሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ጋር በመቀናጀት በወሰደው እርምጃ ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ለመግባት የሞከሩ የሽብር ቡድኑ አመራሮችን ጨምሮ ተዋጊዎቹ ሙሉ ለሙሉ ተደምስሰዋል ነው ያሉት፡፡

የኢፌዴሪ አየር ኃይል የተመረጡ ዒላማዎችን ነጥሎ በመምታት የሽብር ቡድኑ ለረዥም ጊዜ እጠቀምበታለሁ ብሎ ያዘጋጀውን የሎጂስቲክስና ጦር መሳሪያ ክምችት ማውደሙ የተገለጸ ሲሆን ፥ የሽብር ቡድኑን አመራሮችም መደምሰስ መቻሉ ተገልጿል፡፡

ሐምሌ 29፣ 2014 (ኢሳት)

1 Comment

  1. አሁን ጂዋር መሀመድን ቁጀልክጝ ሽመልስ አብዲሳን ሌንጮዎችን አስቀምጦ አልሸባብን ፍለጋ መሄድ ነገር ፍለጋ አይሆንብንም

Leave a Reply

Your email address will not be published.

296312938 604154057905581 1555662693273264556 n
Previous Story

የ“ኢንሳ” ምክትል ዋና ዳይሬክተር፤ ተቋሙን እንዲመሩ ተሾሙ

297800468 5693981423956772 5891905279834163171 n
Next Story

የራያን ሕዝብ ትግል የሁሉም አማራ የማድረግ ተልዕኮ! – ሲሳይ መንግስቴ (ዶ/ር)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop