ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በመጠጥ ቤት ታዳሚዎች ላይ በተከፈተ የእሩምታ ተኩስ 19 ሰዎች ተገደሉ

በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ቀጠና እና በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኙ ሁለት መጠጥ ቤቶች ላይ በደረሱ የእሩምታ ተኩስ ጥቃቶች 19 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ ።

በጆሃንስበርግ ሶዌቶ መንደር ፣ በሚኒባስ ተጭነው የመጡ ጥቃት አድራሾች በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ በመዝናናት ላይ በሚገኙ ሰዎች ላይ የእሩምታ ተኩስ መክፈታቸውን ተከትሎ 15 ሰዎች ተገድለዋል ።

በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ላይ በምትገኘው ፣ ፒተርማሪትዝበርግ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ሌላ መጠጥ ቤት ውስጥ ደግሞ ሁለት ሰዎች ካለ ልዩነት በዚህ በነበሩ ሰዎች ላይ ተኩስ ከከፈቱ በኃላ በነበረ የተኩስ ልውውጥ 4 ሰዎች ተገድለዋል፣ 8 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ።

ፖሊስ ጥቃቶቹ ተያያዥ ስለመሆናቸው ለመናገር ጊዜው ገና መሆኑን ጠቁሞ፣ ተመሳሳይነታቸውን ግን ማጤኑን አስታውቋል-። ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ እንደሌለ ተገልጿል። ሁለቱ ጥቃቶች የደረሱት ፣ ሀገሪቱ ከአፓርታይድ ዘመን ተላቃ ዴሞክራሲን መከተል ከጀመረችባቸው ሶስት አስርት ዓመታት ወዲህ ፣ በእጅጉ የከፋ ነው በተባለ የኃይል ጥቃቶችን እና አለመረጋጋት ሰደድ መመታት በቀጠለችበት ሰዓት ነው።

ባለፈው ሀምሌ ወር ላይ በእጅጉ የተንሰራፋ አመጽ፣ ዘረፋ ፣ በእሳት ማጋየት እና የመሰረተ-ልማት እና ኢንደስትሪ ተቋማትን ባወደመ ጥቃት ወቅት 350 ሰዎች ሞታዋል።በኮቪድ 19 ዳፋ በተፈተነችው ሀገር በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል ። ዘገባው የኤ ኤፍ ፒ ነው።

VOA

ተጨማሪ ያንብቡ:  አርቲስት ታማኝ በየነን ጨምሮ ታዋቂ ግለሰቦች እና የቀድሞ ጦር ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ወደ ግንባር ዘመቱ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share