May 30, 2022
2 mins read

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለሁለተኛ ቀን ፍርድ ቤት ቀረበ – ታሪኩ ደሳለኝ

tEMESGEN
tEMESGEN
በዛሬው ዕለት ግንቦት 22/2014 በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ችሎት ፍርድ ቤት የቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሁለተኛ ቀን ቀጠሮው ፖሊስ ጋዜጠኛውን በምን ወንጀል እንደሚጠይቅ ስላማናውቅ ምርመራው ተጣርቶ ሲያልቅ የሚጠየቅበትን ለመወሰን የተጠየቀው ዋስትና ሳይፈቀድለት ለግንቦት 29/2014 ጠዋት 3:30 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል::
ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ እንዳሉት በምንም ነገር ቢጠየቅ ጋዜጠኛ በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ መሰረት ዋስትናው ትከብሮለት ነው የማጣራት ሂደቱ መታየት ያለበት ሲሉ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፣ ለ30 እስረኞች በተዘጋጀ ክፍል ውስጥ 400 እስረኞች በአንድ ላይ ታስረው በሚገኙበት ክፍል ውስጥ ታስሮ እንደሚገኝ ጠበቃው ለችሎቱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው ችሎት አዲስ ዳኛ የተለወጡ ሲሆን፤ ዳኛው የግራ ቀኝ ሀሳብ ከመስማት ይልቅ ቀጥታ ወደውሳኔ (የቀጠሮ ጊዜ) ሀሳብ መግባታቸው ብዙዎቹን የችሎቱ ታዛቢዎች ያስገረመ ጉዳይ ሆኗል።
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እስራት በነፃ ጋዜጠኝነት ሙያ ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው። የታሰረው አንድ የነፃው ፕሬስ መሪ ተዋናይ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነት ነው።
በኢትዮጵያ የነፃው ፕሬስ ታሪክ ውስጥ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከ13 ዓመታት በላይ ስለፍትሕ፣ ነፃነትና እኩልነት ዘር ቀለም ኃይማኖት ሳይለይ የታገለ የግፉዓን ድምፅ ነው። የጋዜጠኛው እስር የኢትዮጵያ የሽግግር ዴሞክራሲ ለመጨናገፉ አንድ ማሳያ ሆኖ ይቀርባል።
የ Pen2Pen Freedom of Expression Award 2020 ተሸላሚው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የሙያ መርሆዎቹ ፦ ነጻነት፣ ፍትሕ፣ እና እኩልነት፣… ናቸው።
ቤተሰቦቹ እና የፍትሕ መጽሔት ባልደረቦች

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Andualem and christian
Previous Story

የኢዜማው አንዷለም አራጌ እና የአብኑ ክርስቲያን ታደለ የእሮሮና የአቤቱታ ፖለቲካ – ጠገናው ጎሹ

f4e8569bda61082637e051bd7072941e
Next Story

የአማራ ሕዝብና የአጭቤ ዜናው አባት አማራጠሉ ቢቢሲ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop