March 26, 2022
3 mins read

የ’ኤች አር 6600’ ረቂቅ ሕግን የሚቃወም ሰልፍ በሳን ፍራንሲስኮ ከተማ ተካሄደ

277166764 5290928907654514 8013396154406352331 n

277166764 5290928907654514 8013396154406352331 nኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን የተሳተፉበት ’ኤች አር 6600’ ረቂቅ ሕግን የሚቃወም ሰልፍ በካሊፎርኒያ ግዛት ሳን ፍራንሲስኮ ከተማ ተካሄደ።

ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን የተሳተፉበት ሰልፍ የተካሄደው በሳን ፍራንሲስኮ የሕዝብ ቤተ-መጽሐፍት አካባቢ ነው።

እ.አ.አ በ2014 ሕይወቷ ያለፈው የአሜሪካ ገጣሚ ማያ አንጀሎ የመታሰቢያ ሥነ ሥርዓት በቤተ-መጽሐፍቱ የተካሄደ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የአሜሪካ ኮንግረስ አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲና የአሜሪካ ኮንግረስ አባል ባርባራ ሊ(ካሊፎርኒያ) ተገኝተዋል።

ዳያስፖራው ይሄን አጋጣሚ በመጠቀም ’ኤች አር 6600’ ረቂቅ እንደሚቃወሙትና ባለስልጣናቱ ኢትዮጵያን እንዲሁም በኢትዮጵያና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚጎዳውን ሕግ ውድቅ እንዲያደርጉት መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን ኢዜአ በሰሜን ካሊፎርኒያ የኢትዮጵያዊያን ስብስብ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ረቂቅ ሕጉ በአሁኑ ሰአት በኮንግረስ አፈ-ጉባኤዋ ናንሲ ፔሎሲ እጅ ላይ የሚገኝ በመሆኑ አፈ-ጉባኤዋ ሕጉን ለኮንግረሱ እንዳታቀርብ ጥሪ ቀርቧል።

277220021 5290928910987847 3741081350707996562 nሕጉ ኢትዮጵያንና በኢትዮጵያና አሜሪካ ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚጎዳ መሆኑን ልትረዱት ይገባል ብለዋል ሰልፈኞቹ።

በአሜሪካ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ መጋቢት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ‘ኤችአር 6600’ ረቂቅ ሕግን የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በኒው ጀርዚ ሕጉን ባረቀቁት ቶም ማሊኖውስኪ ቢሮ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው።

‘ኤች አር 6600’ እና ‘ኤስ.3199’ ረቂቅ ሕጎችን የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም በዋሺንግተን ዲሲ በአሜሪካ መንግሥት መቀመጫ ‘ካፒቶል ሂል’ ፊት ለፊት ይካሄዳል።

በአሜሪካ የኮንግረስ አባል ቶም ማሊኖውስኪ (ኒውጀርሲ) ዋና አርቃቂነት፣ በያንግ ኪም (ካሊፎርኒያ)፣ ግሪጎሪ ሚክስ (ኒው ዮርክ)፣ ዴቪድ ሲሲሊን (ሮድ አይላንድስ)፣ ብራድ ሼርማን(ካሊፎርኒያ) እና ማይክል ማካውል (ቴክሳስ) ደጋፊነት የተዘጋጀው ‘ኢትዮጵያ ስታብላይዜሽን ፒስ ኤንድ ዴሞክራሲ አክት’ ወይም ኤችአር 6600 ረቂቅ ሕግ በኮንግረሱ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ውይይት እንደተደረገበት የሚታወስ ነው።(ዋልታ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

hr 6600 1
Previous Story

የፓትርያርኩ HR 6600 ላይ ያነጣጠረው ሴራና የጋዜጠኛ አርአያ ያልተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች በስለ ሀገር

eeeef
Next Story

እስክታልቁ ድረስ ስከኑ ይሉናል የአማራ ክልል ፕሬዘዳንት – መስከረም አበራ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop