ሚሊዮኖች ድምጽ – የነጻነት ደዉል በአዲስ አበባ፣ በአዋሳ እና በደሴ ተደዉሏል!

አንድነት ፓርቲ

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችና ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም።

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ መብት እንዳላቸው ይደነግጋል።

“Everyone shall have the freedom, in association with others, to peaceably assemble without arms, engage in public demonstration and the right to petition. Appropriate procedure may be enacted to ensure that public meetings and demonstrations do not disrupt public activities, or that such meetings and demonstrations do not violate public morals, peace and democratic rights.”

ይላል አንቀጹ።

በአዲስ አበባ፣ በደሴና በአዋሳ ሰላማዊ ሰልፎች ይደረጋሉ። በሰልፉ የጥበቃ ኃይላት ያሰማሩ ዘንድ ለባለስልጣናት አስፈላጊዉ የማሳወቅ ደብዳቤ ተልኳል። በታሰበው ቀንና ቦታ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ካሉና በቂ የጥበቃ ኃይል ማሰማራት ባለስልጣናት ካልቻሉ፣ ቀኑ እንዲራዘም ወይንም የሰልፉ ቦታ እንዲቀየር ሊጠይቁ ይችላሉ። ከዚያ ዉጭ ሰልፎችን የመፈቀድም ሆነ የመከልከል መብት ባለስልጣናት የላቸውም። ይሄ መታወቅ አለበት። ከከለከሉ ወይንም መፍቀድ አለብን ካሉ፣ በቀጥታ የአገሪቷን ሕግ ያፈርሳሉ ማለት ነው። ሕገ ወጥ የሚሆኑት እነርሱ ናቸው ማለት ነው።

ሰልፍ ማድረግ አመጽ አይደለም። የአንድነት ፓርቲ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ላለፉት በርካታ ወራት የተለያዩ ሰልፎች አድርገዋል። በሰዉም ሆነ በንብረት ላይ አንድም ጉዳት አልደረሰም። ከፖሊሶች ጋር ምንም አይነት ግብግብ አልተፈጠረም። አንዲት ጠጠር አልተወረወረችም። ኢሕአዴጎች ይሄን ልብ እንዲሉ ያስፈልጋል። እነርሱ ሌላው ሕግ ማክበር አለበት እንደሚሉት፣ ሕግን ማክበሩ ያዋጣቸዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ‹‹መንግሥት ለአገር ሕልውና የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም›› አቶ ግዛቸው ሙሉነህ

እንግዲህ ሁላችንም እንዘጋጅ፤ ዉስጥ ውስጡን ማጉረምረም ይበቃናል። እርስ በርስ ማንሾካሾክ ይበቃናል። ከሚሊዮኖች ጋር ሆነን ድምጻችንን በድፍረት፣ በአደባባይ እናሰማ። ፈርተን እና ተስፋ ቆርጠን ከተደበቅን፣ ከሸሸን፣ ዝምታን ከመረጥን፣ በሙስናና በመልካም አስተዳደር እጦት የተዘፈቁት ገዢዎቻችን የደገፍናቸው ነው የሚመስላቸው። እንነሳ፣ እንቀሳቀስ። ሕገ መንግስቱ ይፈቅድልናል። ኢትዮጵያዊ የዜግነት ግዴታም አለብን።

እኛ ጥይት አንተኩስም ! ጠጠር እንወረወርም! ጥላቻን አንዘምርም። ክርስቲያን፣ ሙስሊም፣ ኦሮሞ፣ ትግሬም፣ አማራ፣ በብሄረሰቡ መታወቅ የማይፈልገው ቅልቅሉ..…ሁላችንም፣  በዘር፣ በኃይማኖት ሳንከፋፈል፣ ሚሊዮኖች ሆነን ድምጻችንን እናሰማለን። በርግጠኝነት የሚሊዮኖችን ጥያቄ ሊንቅ የሚችል ማንም ኃይል የለምም፣ ሊኖርም አይችልም።

እንግዲህ የነጻነት ደዉል በአዲስ አበባ፣ በአዋሳ እና በደሴ ተደዉሏል። ጥሪ ቀርቧል። ትኩረቱ ወደነዚህ ከተሞች ይሆናል!!!!!

በላስ ቬጋስ፣ በአትላንታ እና ዴንቨር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እነዚህ ሶስት ከተሞችን ስፖንሰር በማድረግ ድጋፋቸውን በመግለጻቸዉ ሊመሰገኑ ይገባል። ሌሎቻችንም ተደራጅተን፣ ሶሊዳሪቲ በማሳየት የሚሊዮኖች አንዱ እንሁን !

 

እንበርታ ፣ እንጎብዝ ! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

millionsforethiopia@gmail.com

1 Comment

  1. That is the way it should be UDJ! Heartfelt gratitude to Ethiopians in the diaspora ( sponsors) !! I have a great feeling that things look that the days of suffering are numbering, and the days of realistic and serious march for genuine freedom are progressively approaching!!

    >Yes, we are in a critical moment of defeating the notorious and monstrous fear that has terribly challenged us for a long ,long time.
    > Yes, it is time now not only decry the horrible crisis we have faced and continue to face but most importantly to take our powerful words of ENOUGH IS ENOUGH seriously and interpret it into a material force!
    >Yes, the very self-dehumanizing mentality of we live in peace simply because we do not hear and see the terrible noises of killing machines( guns and bombs) .
    > Yes, it is a very self-dehumanizing mentality to hear our innocent citizens saying that they are better of living on begging instead of challenging and confronting those ruling elites who have made them live the live that is much worse than other non-social animals .And we have to do something about it!
    >Yes, a mother who sends her starving children to school just not to see them being terrified in front of her eyes all day must be told that that is not the very essence of peace at all.
    > Yes, millions of parents who go to bed with empty stomachs ( starving to their bones) should be told that that is not the very meaning of living with dignity!
    >Yes, those religious leaders and teachers and servants ought to unequivocally be told that they cannot continue with their preaching that is not practically relevant to the very teaching of Jesus Christ Who has taught and died on the Cross because He has firmly stood with the underdogs !
    >Yes, those teachers of all levels of educational institutions need to clearly be told that their education can only and only make sense if they use that weapon against the catastrophic situation the country and her people are facing!
    >Yes, those who involve in any kind of business must be told with on reservation that they cannot afford to continue being victims of highly chronic corruption and the economy of ethnic-based cronyism !
    >yes, those who are the beneficiaries of the very evil-driven political and socio-economic cronyism , if not deadly partnership with the inner circle of the ruing party TPLF/EPRDF must be told to come back to their common human senses and side with the people before it is too late!!
    >yes, the young generation has to strictly be told that it cannot afford to continue watching its future being trapped and killed by those evil-minded politicians!
    And so on and so forth…..
    All the best !!

Comments are closed.

Share