ነፃነት እንፈልጋለን ያሉ ሴት እህቶች በአደባባይ ተቃውሞ ካሰሙ በኋላ 6ቱ ወዲያው ታሰሩ (የተቃውሞውን ቪድዮ ይዘናል)

ሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊው ከሴቶቹ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ቡድን እንደዘገበው ዛሬ በተካሄደው የሴቶች 5ሺሜትር ሩጫ ላይ የሰማያዊ ፓርቲ የሰቶች ጉዳይ ባመቻቸው እድል የፓርቲው ሴቶች የሮጡ ሲሆን በሩጫውም ላይ የተለያዩ መፈክሮች ማለትም ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ትፈታ፤ አቡበከር ይፈታ፣ እስክንድር ይፈታ፣ አንዷአለም ይፈታ፣ ነፃነት እንፈልጋለን እና ሌሎች ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች አሰምተዋል::

ከመነሻው የጀመረው የተቋውሞ ድምጽ እስከ ማብቂያው የቀጠለ ሲሆን ሩጫቸውን ጨርሰው ሊገቡ ሲሉ በፖሊሶች ተቆርጠው በአሁኑ ሰዐት ታስረው ይገኛሉ። በሩጫው ወቅት ተቋውሞ ሲያሰሙ የሚያሳይ ቪድዮ እና ፎቶ እንደደረሰን ምንለቅ መሆኑን በትህትና እንገልጻለን::

የሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሴት አባላት እና ከእናርሱ ጋር የነበሩ ሴቶች በዛሬው እለት በተካሄደው ሩጫ ላይ ተሳትፈው ሃሳባቸውን በመግለጽ ላይ አንዳሉ በሩጫው መጨረሻ ላይ በፖሊስ ታፍሰው ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአከባቢው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ብርሃኑ እና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊው አቶ ጌታነህ ሴቶቹ መታሰራቸው ምንም አግባብነት እና ህጋዊ መሰረት የለውም በማለታቸው ከሴቶቹ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የእስረኞች ስም ዝርዝር
1 ንግስት ወንድይፍራ(የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ)
2 ወይንሸት ሞላ (የምክርቤት አባል)
3 ወይኒ ንጉሴ(አባል)
4. እመቤት ግርማ(አባል)
5. ሜሮን አለማየሁ (አባል)
6. ምኞት መኮንን(አባል)

ለጊዜው የሴቶች ጉዳይ እና የህግ ጉዳይ ኮሚቴ የሆኑት ኢየሩስ ተስፋው እና ኤልሳ ወሰኔ ያሉበትን ልናውቅ አልቻልንም፡፡
ከነዚህ ሴቶች በተጨማሪም በቦታው የነበሩት የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አቶ ብርሀኑ ተ/ያሬድ ፤ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊው አቶ ጌታነህ ባልቻ እና የህዝብ ግንኑነት ኮሚቴ አቶ አቤል ኤፍሬም ናቸው፡፡
እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ አቤል ኤፍሬም በአካባቢው ስለነበሩ ብቻ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ያሉበትን ለማጣራት የሰማያዊ ወጣት ክንፍ አባላት በእንቅስቃሴ ላይ መሆናችንን እያስታወቅን የደረስንበትን ይፋ የምናደርግ መሆኑን እናስታውቃለን፡
ትግሉን በእስራት እና በግድያ ማስቆም አይቻልም::

ተጨማሪ ያንብቡ:  Sport: ኃይሌ ገ/ሥላሴ በ2007 ለወርቅ ሜዳሊያ ሣይሆን ለፓርላማ መቀመጫ ይሮጣል

2 Comments

  1. I am a women and I understand what they are going through. Luck of employment in Ethiopia has sent more than 200 thousands young women to out side the country and face many difficulties, raped, tortured, prisoned and killed by those who employed the poor girls, in the country you need to be a member of TPLF if you say no there is no job for no one.

    The international community keep ignoring the seriousness of the issue, the government continue its ill treatment on the nation. Of course people will have enough in one stage.

  2. @Nancy

    I am an Ethiopian women too, I can understand more about the politics of my country. If the women of Ethiopia does not find work they should not go out protesting towards Eskinder Nega and other journalist who are serving a sentence according to their guilt. I can agree rape victim, inequality, discrimination but they are used by G-7 the messenger of EGYPT. The Egyptian leaders are starting to divide Ethiopia viciously than ever before we have to be united. We have to be free from the EGYPTIANS FIRST.

Comments are closed.

Share