በዳላስ የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ወጣት ኢትዮጵያዊት ናት ተባለ

(ዘ-ሐበሻ) የዳላስ/ቴክሳስ ሚዲያዎች ትናንት ቅዳሜ በፌር ፓርክ አካባቢ የአንድ ሰው ሕይወት መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ መጥፋቱን ዘግበው ነበር። የዘ-ሐበሻ የዳላስ ምንጮች እንደጠቆሙት ከባቡሩ ጋር በመኪና ተጋጭታ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ናት።

የዳላስ ፖሊስ ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫው ባቡሩ መንገዱን በሚያቋርጥበት ወቅት መብራቶች እና ደውሎች እየተሰሙ የነበሩ ቢሆንም መኪናው ውስጥ የነበረ ሹፌር ይህን ደውልና መብራት ባለማስተዋል በሚያቋርጥበት ወቅት አደጋው ደርሷል። ከዳላስ በደረሰን መረጃ መሠረት በዚህ አደጋ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ስትሆን ስሟም ሜላት ማሞ እንደሚሰኝ ከፎቶ ግራፏ ጋር የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በዳላስ ፖሊስ መረጃ መሠረት የተሳፋሪዋ ባቡሩና መኪናዋ በፈጠሩት ግጭት የተሳፋሪዋ ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል። ይህን ተከትሎ በዳላስ ያሉ ኢትዮጵያውያን በወገናቸው ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

እንደፖሊስ መረጃ ባቡሩ 24 ሰዎችን ይዞ ይጓዝ የነበረ ሲሆን ማንም ሰው ወደ ሆስፒታል ባይወሰድም 4 ሰዎች ጉዳት ደርሶብናል ብለዋል።

ሜላት ሃገሯን እና ወገኗን ወዳድ እንደነበረች የሚያውቋት የሚመሰክሩ ሲሆን በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰን ጥቃት ተከትሎ በዳላስ በተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ድምጿን ስታሰማ ነበር። (ፎቶው ከታች አያይዘነዋል)።

ፈጣሪ ነብሷን በገነት እንዲያኖረው ዘ-ሐበሻ በዚህ አጋጣሚ ሃዘኗን ትገልጻለች።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች

12 Comments

  1. If I remember correctly this girl was very emotional in voicing her
    Opinion on the Dallas demonstration for Saudi victims
    Perhaps some weyane agents or Saudi agent killed her and
    Left her in the car on the railroad track to make it seem like an
    Accident? Surely if she was alive, she would try to save her life with all the warning alarms….very strange

  2. ቆንጂዬ እግዜር ለነብስሽ እረፍትን ለወላጆችሽ መጽናናትን ይስጥ

  3. እግዚአብሄር ረዳትዋና መታመኛ የሆነ አምላክዋ ነፍስዋን በገነት ያኑርልን፣፣

  4. meluye you were different than everyone.im not saying this because….you truly were different. I personally know how match you helped your brothers and sisters(Ethiopians) while you are alive.. you will always be remembered may almighty god rest your soul in peace.

Comments are closed.

Share