ቴዲ አፍሮ በሱዳን ለመሐመድ ወርዲ በተዘጋጀ የመታሰቢያ ዝግጅት ላይ በአረቢኛ አቀነቀነ

/

(ዘ-ሐበሻ) “የፍቅር ጉዞ” በሚል በሙዚቃዎቹ ፍቅርን ይሰብካል በሚል የሚወደሰው ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በሱዳን ካርቱም የፊታችን አርብ ፌብሩዋሪ 21 እና እሁድ ፌብሩዋሪ 23 ሁለት ታላላቅ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን እንደሚያቀርብ ከዚህ ቀደም መዘገባችን አይዘነጋም። ቴዲ ለዚህ ኮንሰርት ሱዳን ከገባ በኋላ በካርቱም ለዝነኛው የሱዳን ድምጻዊ መሐመድ ወርዲ በተዘጋጀው የመታሰቢያ በዓል ላይ “ሰበርታ” የተባለውን ተወዳጅ የሱዳን የአረቢኛ ዘፈን በድንቅ ሁኔታ ተጫውቶታል።

ባለቤቱ አምለሰት ሙጬን ከፊት ለፊት አስቀምጦ ለሱዳናውያኑ ያቀነቀነው ቴዲ ከፍተኛ አድናቆትን አግኝቷል። የኢትዮጵያ ሙዚቃዎች በሱዳን በጣም የሚወደዱ ከመሆናቸውም በላይ በተለይ ከ8 ዓመት በፊት ሱዳን የነበረው የዘ-ሐበሻ ዋና አዘጋጅ ሱዳኖች ለቴዎድሮስ ካሳሁን እና ለሃይማኖት ግርማ ልዩ ፍቅር እንደነበራቸው በአይኑ ማየቱን ያስታውሳል። ድምፃዊት ሃይማኖት ግርማ “ዞል ቲቪ” በሚባል የቴሌቭዥን ጣቢያ የፕሮግራም አቅራቢ ሆና እንደነበርም ያስታውሳል።

በካርቱም ቴዲ የፊታችን አርብ እና እሁድ ሥራዎቹን የሚያቀርብ ሲሆን፤ በመሀመድ ወርዲ መታሰቢያ ላይ የተጫወተውን ሰበርታ ሙዚቃ እንጋብዛችሁ፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ዘመነ ካሴን ፍቱት፣ የአማራ የሽምግልና ክብርም ወደ ቦታው መልሱት" - አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ከግንባር

5 Comments

  1. why even go to Sudan? if the The Sudan government has a gut to take the precious land Ethiopia, an artist like Teddy should have boycotted Sudan in general. we have to show our opposition in any way possible. and artists like Teddy have even a bigger resposbility to show their unity to their country people. i understand paying teribute to the dead artist…but his death mean nothing when compare to losing peace of our land. We need to think about those who lose their livelyhood because their land was given away to Sudan. Teddy it is a shame you couldn’t live up to our expectation!

  2. አስገራሚ በሆነ መልኩ ተጫውቶታል የኦዲንሱ ዲሞኒስትሪትም በጣም አስደናቂ ነው በጣም ደስ የሚል ነው

  3. Tedi has very little role to get involved in the twisted Ethiopian Politics. All he needs to do is what he knows best. To reach out with his music beyond and within Ethiopia to unite people.

Comments are closed.

Share