February 5, 2022
22 mins read

የናዝሬት ከተማ  መሥተዳድር የማፍረስ ዘመቻ ና የጉዳቱ ሰለባዎቹ ቅሬታ ! ! – ሲና ዘ ሙሴ

ሰሞኑን በመንገድ ዳር የተገነቡ ና ከመንገድ ዳር ከፕላን ውጪ የተገነቡ የንግድ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ በአዳማ አንዳንድ ቀበሌዎች እየተካሄደ ነው ። የማፍረስ ዘመቻውንም እያከናወነ ያለው የከተማው አሥተዳደር ፤ ይሁን እንጂ  ማዘጋጃ ቤቱ ይሁን ፣ የአሥተዳደር አካሉ የትኛው የማፍረስ ሥራውን እንደሚያከናውን ፣ ባለ ንግድ ቤቶቹ አያውቁም ። አብዛኛዎቹም ከግለሰብ ተከራይተው ሥለሚሰሩ ፣ ግርግሩ ግራ አግባቷቸዋል ።  በግልፅ የሚያውቁት ጉዳይም የለም   ። አፍራሽ ግብረ ኃይሎችም ፣  ለፀጥታና መረጋጋት ይበጃሉ ተብለው ከየጎጡ የተመለመሉ እጅግ የበዙ ሥራ አጥ ዜጎች  ናቸው ። ( አንዳንዶቹም የቀበሌ ቤት እናገኛለን ብለው ፣ የቀን ሥራቸውን ትተው ከቀበሌ የብልፅግና ካቢኒዎች ጋር ዘወትር የሚባትሉ ናቸው ።

በእርግጥ ከአፍራሾቹ ውሥጥ   አንዳንድ የመሥተዳድሩ አካላትም በብልፅግና ሥም ራሳቸውን የሚያበለፅጉ ቀምቶ በሎች እንጂ ሠርቶ በሎች እንዳልሆኑ ስለሚታወቅ በዚህ ተግባር ላይ መሠማራታቸው ፈፅሞ አያሥገርምም   ።

እናም እላለሁ ፣ “   ይኽ የማፍረስ ዘመቻ   የሥራ ፈቶች ዘመቻ በመሆኑ አንድ ታታሪ ሰው ፣ ምን ያህል እንደሚለፋ እና ለኑሮዎ መቃናት እንደሚደክም ያልተገነዘበ በመሆኑ በአሥቸኳይ መቆም አለበት ።  በማፍረስ እና መልሶ ጉቦ ተቀብሎ ማሰራት ፣ እንደ ወያኔ ዘመን ልማድ ዜጎችን ማሥከፋት ነው   ይገፀስ  ። ይኼ ፣ ትላንት ያሥተዋልነው ፤ ውሃ ቅዳ ፣ ውሃ መልስ ተግባር ነው  ። ይኽ የማፍረስ ዘመቻ በሥራ ለምናምን ብዙዎቻችን አሥከፊና ግማሽ ልጩ ና ገማሽ ጎፈሬ የሆነ  ድህነትን አሥፋፊ   ዘመቻ በመሆኑ በአሥቸኳይ ይታረም ። “ እላለሁ  ።

ይኽ  ድህነትን የሚያበረታታ ፣ የማፍረስ ዘመቻ ፤ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ያለው   ፣  በየመንገዱ ዳርና ዳር ፣ ከተከራዩበት ቤት ውጪ ፣ ጊዚያዊ  ጥላ ሰርተው ፣ ቤት ገንብተው ፣ የፀሐይ መጠለያ ሰርተው ሸቀጦቻቸውን   ዘርግተው ፣ እየሸጡ ባሉ ግለሰቦች እና እነሱን ከለላ አድርገው ፣ ሲኒ ደርድረው ቡና በመሸጥ ላይ የነበሩትን በእጅጉ የሚጎዳ ና ወደ ድህነት አዘቅት የሚጨምር ነው ና መወገዝም አለበት  ።

በዋና መንገድ ላይ ወንበር ደርድረው ፣ ይኽንን ደሃ ህዝብ ሥጋ እየበሉ ና ውስኪ እየጠጡ  የሚያሥጎመጁትን ፣ “ ወደ ንግድ ቤታችሁ ግቡና ያሻችሁን ፈፅሙ ። ይኽ ነፃ ቦታ የእናንተ በረንዳ አይደለም ና በህዝብ መተላለፊያ ላይ ተቀምጣችው ፣ ህዝብን አታሳቁት ፤ አታሰቅቁት ፣ …  ።”  በማለት የወሰዳችሁት እርምጃ ተገቢና ትክክል ቢሆንም ፣ ሁሉንም ቀበሌዎች በነካ እጃችሁ መዳሰሱን አትዘንጉም ። ይላል ህዝቡ ።

ለውበት አሳማሪ _ ሊስትሮዎችና ለመንገድ ላይ ቡና አፍይዎች የተዋበ መጠለያ በጎዳና ላይ ወይም  ጥገ አላይም በፓርክ ውሥጥ ቦታ ሰጥቶ  ሥራ አጥነትን ፣ ሥራ በመፍጠር ፣ ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ የማይጥር ፤ የከተማ አሥተዳደር ፣ ለብልፅግና ቆሜያለሁ ማለት አይችልምና ይኽ የማፍረስ ፣ ህዝብና መንግሥትን የሚያቀያይም ተግባር በነማን ውጥን እና ምክር እንደተከናወነ ይጣራ   ?

ህዝብ የሚለው ፣ “ የከተማው መሥተዳድር ፣ ነገ ከተማው ሲለማ ፣ ፎቅ እየተሰራ ቅርፅ በሚይዘው ከተማ ፣ ምንም ዓይነት እግረኛ የማይጎዝበትን  ፣ በጭርንቁስ ቤት የተሞላን የጎዳና ዳርና ዳር ፣ ዳስና በረንዳ ማፍረሱ ተገቢ ና ፍትሃዊ አይደለም ። “ ነው ። ለዚህ ድህነትን የማሥፋፋት ፣ ድርጊትም የምንጃር ጎዳናንን በዋቢነት ያቀርባል   ።     “ በተለይም  08 እና 07  ቀበሌ ውሥጥ የሞሉት ጭርንቁስ ቤቶች በጊዚያቸው በልማት የተነሳ መፍረስ ላይቀርላቸው ለምን ዛሬ ብዙ ሺ ሥራ አጦችን በውሥጣቸው አካተው ሣለ በዘመቻ መልክ የማፍረስ ተግባር ሊከናወንባቸው ቻለ ?  “ በማለትም ይጠይቃል ።

እነዚህ ሁለት ፣ ቀበሌዎች ያለሙና  እጅግ የበዛ ህገወጥ ግንባታ ያለባቸው ናቸው ። 08 ሙሉ ለሙሉ የህገወጥ ገብያ መናህሪያ ነው ። ሙሉ ለሙሉ ” ጉልት ነው ።” ማለት ይቻላል  ። ዜሮ ሰባትም ከ08 የማይሻል የምንዱባኖች የዕለት እንጀራ ማግኛ  ቀበሌ ነው ።

እነዚህ ሁለቱ ቀበሌዎች ፣ የሚለወጡት ፣ በአገሪቱ ሠላምና መረጋጋት ሰፍኖ ፣መንግሥትና ህዝብ ወደልማት ፊቱን ሲመልስ እንደሆነ ይታወቃል ።በወቅቱ  በልማት ፣ ሥለልማት ከተባለ ደግሞ ፣ ለጉልት ቸርቻሪዎች ፣ ሌላ ህገዊ ሆነው የሚሰሩበት ፣ እራሳቸውን ጠቅመው አገሪቱንም በግብር ክፍያ የሚጠቅሙበትን ፣ መንገድ በማመቻመች  ቸርቻሪዎቹን ወደ ሌላ የገብያ ማዕከል መጠለያ ( ሼድ ) ሰርቶ ማዛወር እንጂ ፤  ብት ፈልጉ ዲንጋይ ብሉ ብሎ ፣ ከየጉልቱ ጠራርጎ ማንሳት የሚፈጥረው የራሱ የማይቀለበስ ችግር እንደሚወልድ የታወቀ ነው ።  እናም  ተለዋጭ  ሥፍራ  ሳያዘጋጁ  መነካካት አላሥፈላጊ አይመሥለኝም ። ለራሱ ሰው ኑሮ ጭቅላቱን አዙሮታል ። ተጨማሪ ትንኮሳ ፣ ሆድ ለባሰው ጩቤ ማዋስ እንደሆነም መንግሥት አያውቅም ማለት አይቻልም ።

“ትላንት  ፣ በአማራና  አፋር የደረሰውን መፈናቀል እኛም እንደግመዋለን ! ” ነው እንዴ ነገሩ ? … ።በበኩሌ ፣ “ ይኽ የማፈናቀል ዘመቻ ፣ ህዘብን ለማስቀየም እና የብልፅግና መንግሥትን የድህነት መንግሥት አድርጎ ለመሣል የተወጠነ ነው ። ሌበነት ፣ ለማኝነት ፣ ጎዳና ተዳዳሪነትን  ለማበራከት እና እንደገና በሁከትና በብጥብጥ መንግሥት እንዲተረማመስ  ና ሀገር እንዲፈርስ ለማድረግም በህግ ማሥከበር ሥም የተተኮሰ የመጀመሪያው ሠላም አደፍራሽ ጥይት ነው ። “ ብዬ ለማመን እገደደለሁ ። ይኽ  ድርጊት  መወገዝ ያለበትና በአስቸኳይ መቆም ያለበት ውጉዝ ተግባር  እንደሆነም አሰምርበታለሁ ።

ይኽ ውጉዝ ተግባር ፣  በእግረኛ መንገድ ማፅዳት ሥም ፣  በመሐል ከተማ በጎርፍ መውረጃዎች ውሥጥ የተከማቸውን ግማት ፣ ማዘጋጃ ቤቱ  ሳያፀዳ ፤ በሥራ ፈትነት አልያም ለሥውር ጥቅም ፣ አልያም ለሥውር ሤራ  የገባባት የማፍረስ ተግባር  ከሆነ ደግሞ እጅግ አሣፋሪ ነው ።

( እኔ የለሁበትም የየቀበሌው ካድሬዎችና አጫፈሪዎቻቻቸው ናቸው ካለ ደግሞ ፤  በማዘጋጃ ቤቱ አንፈርድም ። )

እንዴ ! ሆን ብሎ ሠርቶ የሚበላውን ህዝብ ፣ የመሥሪያ ሥፍራውን እያፈራረሱ ፣ መሥለቀሥ ምን የሚሉት ህግና ደንብ ማሥከበር ነው ?  ለሚሰራ ሰው ቀድሞ ቦታ ሳያመቻምቹ   እነሱን ተገን አድርገው የዕለት እንጀራቸውን የሚያገኙትን የመንገድ ላይ ቡና አፍይ እህቶቻችንን እንጀራ መሣጣትሥ  የሚጨበጨብለት ተግባር ነውን ? ¡¡ ከምናፈናቅላቸው በፊት  ለሠራተኛ ዜጎች  ተገቢ መፍትሄ ማሥቀመጥ የአሥተዳደር ነኝ ባዩ ፤ የመንግሥት ሹም ኃላፊነት ነበር ። ይኽ አሥተዳደር የመንግሥት የታችኛው አካል መሆኑንም መዘንጋት አልነበረበትም ።

ዜጎች  ይህ  የታችኛው  የመንግሥት አካል ፣ ፖሊሥን እና ሥራ ፈት የጎጥና የቀበሌ ጭፍራዎቹን ይዞ ” ኃይ በለው ” በማለት በዘፈቀደ ፣ ከጎዳና ላይ ዜጎችን “ቢፈልጉ አፈር ይብሉ ። ምን አገባኝ ። አሥጨንቄ ኋላ ትርፍ አገኛለሁ ። …”በማለት መንቀሳቀሱን ያውቃሉና ፣ ቅሬታቸው አገርን በመምራት ላይ ባለው መንግሥት ላይ መሆኑንን ከፍተኛው የመንግሥት አካል ማወቅ አለበት ። ብዙ መልካም አማራጮችን እና ገቢዎችን ማግኛ መንገድ እያለ ፣ በደቀቀ ኢኮኖማ ፣ ዜጎችን በሥራ አጥነት ማድቀቅም ነውረኝነት ነው ። መሥተዳድሩ ድብቅ ሤራ ባይኖረው ፣ ወይም የዕውቀት ደሃ ባይሆን ኖሮ ፣ ዜጎች ፣ ባልተገነነ ኪራይ ፣ ሰርተው የሚለወጡበትን ፣ የመንገድ ጥግ  ፣ ቡና ማፍያ  ፣ በአማረ መልኩ ሠርቶ በማከራየት ፣ ማዘጋጃቤቱ ገቢ ማግኘት ይችል ነበረ እኮ ! !

ለምሳሌ ፣ ለጫማ ውበት ጠባቂዎች ፣ መንገዱን የሚያሥውብ የፀሐይ መከላከያ ና መቀመጫ ፣ በየመንገዱ በመሥታወቂያ አገልግሎት ፣   በየመቶ ሜትሩ በማሠራት ፣ ለማዘጋጃ አገልግሎት     ፣ በየወሩ በባንክ  እንዲከፍሉ በማድረግ ገቢውን ማሳደግ ይችል ነበር ። ህዝብን ዝቅ ብለው በማገልገል ፣  የዕለት እንጀራቸውን  በማግኘት  ላይ ያሉትን ፣ አገርን ጠቃሚ ማድረግ ሲገባ ፣ ማሳደድ ተገቢ ና ትክክል አይደለም ። በዚኽኛው ዳር መንገድ ላይ ቁጭ ብሎ ሲሰራ ” የእኔ ወገን ነው ። ”  ብሎ መተው ፣ በወዲያ በኩል ተመሣሣይ ሥራ የሚሰራውን በነጋ በጠባ ” መጣሁብህ !  ንብረትህን እወርሳለሁ !! ” ብሎ ማሥፈራራት የሰው ተግባር አይደለም ና ሊወገዝና ባሥቸኳይ እንዲቆም ቀጭን ትዕዛዝ በሚመለከተው ባለሥልጣን ሊሠጥበትም  ይገባል ።  …

( በአዳማ ከተማ ፣ በዋናው ንግድ ባንክ ፊት ለፊት ፣ በፓርኩ  መሐል ፤ በኮብል እስቶን መንገዱ ጥጉን ይዘው የሚሰሩትን ሊስትሮዎች ፣ እንዳይሰሩ መከልከል በበኩሌ ፣ ዘርፋችሁ ፣ ሠርቃችሁ ፣ ለምናችሁ ወዘተ ። ብሉ እንጂ ሠርታችሁ አትብሎ ማለት ነው ።

ሥለ ህገ ወጥ አሠራር መወገድ ከተነሳ   ፣ ከወያኔ አገዛዝ ጀምሮ ህግን መጣሥ የተለመደ እና የሚበረታታ ሆኖ መገኘቱ እየታወቀ ። በዋነኝነት ይህን የህገ ወጥ መድረክም የከፈቱትና ለመላው ከተማ ኗዋሪ ያሥተማሩት  እነሱ መሆናቸው እየታወቀ ፣ ዛሬ ደርሶ ይህንን ውሥብሥብ ህገ ወጥ ድርጊት ፣ ህጋዊ ና ሁሉንም ያካተተ ባልሆነ የጉልበት መንገድ ፣ ቦታ እየለዩ  ማፍረስ ህገ ወጥ አሠራር ነው ። በቅድሚያ ሊታሰብበት የሚገባው ጉዳይ ፣ ለእነዚህ ህገ ወጥ ድርጊቶች ፣ ምን ዓይነት ህጋዊ መፍትሄ በናቅድና ፣ይህንን እቅድ ለመተግበር የሚያሥችል ሀብት ከነማን እናገኛለን ብሎ ማሰብ ሊቀድም ይገባል ። ለሁሉም ነገር ፣ ለከተማ ፅዳቱም ቢሆን በቆሻሻ ለተሞላው አርጂን ዘላቂ መፍትሄ ለመሥጠት ፣ በችግሩና በችግሩ አፈታት ዙሪያ የሚመለከታቸውን ምሁራንን ያካተተ ውይይትና እቅድ እጅግ አሥፈላጊ ነው ።

የከተማ ውበትና ፅዳት የሚመለከታቸው ና የሚቆረቁራቸው ፣ የበኩላቸውን ለማዋጣት ዝግጁ የሆኑ ምሁራን ከተማዋ አላጣችም ።  ደግሞም መታወቅ ያለበት ፣  መላ አዳማ ፣ በአራቱም አቅጣጫ ፣  በጨረቃ ቪላ ቤቶችና ደሳሳ ጎጆዎች  የተሞላች ፣ እና የአካባቢውም ውበት ፣ በእጅጉ የቆሸሸበት ሥፍራ   መኖሩ እንግዳ አይደለም ። እናም  ህገ ወጦች ባለ ጨረቃ ቤቱች ፣  ቢያንስ ግብር የሚገብሩበትን መንገድ መመቻቸት ወይም ወደ ህጋዊ መንገድ ማምጣት እንዲቻል የመፍትሄ አቅጣጫ ሊያሥቀምጡ የሚችሉት እነዚህ ምሁራን እንደሆኑ መገንዘብ ያሥፈልጋል  ።  ቆሻሻ በሚከማችበት የጎርፍ መውረጃም ከአካባቢው ባለሀብት ጋር በመነጋገር ፣ የጎርፍ መውረጃው ፣ ቆሻሻ በማይደፋበት መልኩ ፣ በወጉ  የማገነባበትን መንገድ ሊቀይሱ የሚችሉት እነዚህ ምሁራን ናቸው  ።

ይኽን የከተማዋን ገፅታ ያበላሸ ፣ ማሀል ከተማ ውሥጥ የሚታይ አሥጠሊታ ቆሻሻ ለማሶገድ ፣ መላው የከተማን ህዝብ አሥተባብሮ ወደ መፍትሄ መግባትን ተቀዳሚ ሥራው ከማድረግ ይልቅ ነገ በልማት አሥገዳጅነት የሚሥተካከሉትን እና ከሥራቸው ጋር የብዙ  ሺ ሠርቶ በሌዎችን ጉሮሮ የሚያረጥቡ ፣ የሥራ መድረኮችን መዝጋት በአሁኑ ሰዓት በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነውና የብልፅግና መንግሥት ድህነትን ከማሥፋፋት  ና በፀሐይና በቁር አቦራ ለብሰው ጎንበስ ብለው ጫማችንን በማሣመር የሚተዳደሩትን ሊስትሮዎች እና ትኩስ ቡና ለደሃው አዘጋጅተው በርካሽ ዋጋ ጀባ የሚሉንን ወደ ድህነት አረንቋ ተመለሠው እንዲገቡ ከመጫን እንዲቆጠብ በፅኑ እንመክራለን ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

እመኑኝ፣ “ኦሮምያ” የተፈጠረችበትን ቀን ትረግማለች! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

w11221rr
Next Story

ግርማዊ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘኢትዮጵያ የአፍሪካ አባት (ተረፈ ወርቁ ደስታ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop