January 10, 2022
6 mins read

“ውሳኔው እየመረረን የዋጥነው እውነታ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

271667649 470140381306950 8693962778430973957 nጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙ ሰዎችን ክስ በማቋረጥ ከእስር እንዲለቀቁ በመንግሥት በኩል የተደረሰው ውሳኔ ቁጣን የቀሰቀሰ መሆኑን እና መወሰድ የነበረበት እርምጃ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ።

ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ለአገራዊ መግባባት አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር በሚል የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲዎች አመራሮችና አባለት እንዲሁም የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ክስ ተቋርጦ ከእስር እንዲወጡ መደረጉ ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ የአንዳንዶቹን ከእስር መለቀቅ በተመለከተ ከተለያዩ ወገኖች ተቃውሞና ጥያቄ ሲቀርብ ተሰምቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት እሁድ አዲስ አበባ ውስጥ በተካሄደው አዲሱ የመከላከያ ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር በመንግሥት ውሳኔ ላይ የተሰማውን ተቃውሞ አንስተው ምላሽ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ጉዳይ “እኛንም መጀመሪያ ስንሰማው ያስደነገጠ ነው” በማለት፣ “ነገር ግን ቀኙን ስንፈትሽ ለኢትዮጵያ የሚበጅ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም የሚያግዝ፣ የኢትዮጵያን ጠላቶች የሚቀንስ፣ በአውደ ውጊያ ያገኘነውን ድል በሰላሙ መድረክ እንድንደግም የሚያደርግ ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሸነፉ ያሏቸው ኃይሎች “ክስ እንዲቋረጥ እና ከእስር ቤት እንዲወጡ ሲደረግ ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል” በማለት ይህም ቁጣ ከሁለት ወገኖች መሰንዘሩን ጠቅሰዋል።

አንደኛው ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ሲኖር የማይደሰቱ ያሉት ሲሆን፣ “የት እንዳሉ የማይታወቁ . . . አጓጉል ብልጣብልጥነት የሚያጠቃቸውና እምብዛም ጆሯችንን የማንሰጣቸው” በማለት አጣጥለዋቸዋል።

ሁለተኛው ቡድን ደግሞ በዜናው ድንገተኝነት የደናገጠ “ለአገሩ ሁሉን ነገር ያበረከተ . . . ይህንን እኩይ ጠላት አምርሮ የሚጠላ እና ከዚህ ጠላት ጋር የሚደረግ ማንኛውም ንግግር ኢትዮጵያን ይጎዳል ብሎ የሚያምን ቅን ተቆጪ ነው” በማለት ይህንን ወገን መንግሥታቸው “ሙሉ በሙሉ ይረዳል፣ ያደምጣል፣ ለማስገንዘብም ጥረት ያደርጋል” ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት እሁድ አዲስ አበባ ውስጥ በተካሄደው አዲሱ የመከላከያ ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር በመንግሥት ውሳኔ ላይ የተሰማውን ተቃውሞ አንስተው ምላሽ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ጉዳይ “እኛንም መጀመሪያ ስንሰማው ያስደነገጠ ነው” በማለት፣ “ነገር ግን ቀኙን ስንፈትሽ ለኢትዮጵያ የሚበጅ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም የሚያግዝ፣ የኢትዮጵያን ጠላቶች የሚቀንስ፣ በአውደ ውጊያ ያገኘነውን ድል በሰላሙ መድረክ እንድንደግም የሚያደርግ ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሸነፉ ያሏቸው ኃይሎች “ክስ እንዲቋረጥ እና ከእስር ቤት እንዲወጡ ሲደረግ ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል” በማለት ይህም ቁጣ ከሁለት ወገኖች መሰንዘሩን ጠቅሰዋል።

አንደኛው ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ሲኖር የማይደሰቱ ያሉት ሲሆን፣ “የት እንዳሉ የማይታወቁ . . . አጓጉል ብልጣብልጥነት የሚያጠቃቸውና እምብዛም ጆሯችንን የማንሰጣቸው” በማለት አጣጥለዋቸዋል።

ሁለተኛው ቡድን ደግሞ በዜናው ድንገተኝነት የደናገጠ “ለአገሩ ሁሉን ነገር ያበረከተ . . . ይህንን እኩይ ጠላት አምርሮ የሚጠላ እና ከዚህ ጠላት ጋር የሚደረግ ማንኛውም ንግግር ኢትዮጵያን ይጎዳል ብሎ የሚያምን ቅን ተቆጪ ነው” በማለት ይህንን ወገን መንግሥታቸው “ሙሉ በሙሉ ይረዳል፣ ያደምጣል፣ ለማስገንዘብም ጥረት ያደርጋል” ብለዋል።

BBC

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop