December 16, 2013
3 mins read

(ሰበር ዜና) የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ባለበት በገለልተኛነቱ እንዲቀጥል ተወሰነ

(ዘ-ሐበሻ) በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ታላላቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አንዱ የሆነው የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ለረጅዥም ጊዜ ምዕመናኑን በሁለት ሃሳብ ከፍሎ ሲያወዛግብ የቆየው በሃገር ቤት ያሉት አባቶች እና በውጭ የሚገኙ አባቶች አንድነት እስኪያመጡ ድረስ በገለልተኝነት እንቆይ እና፤ ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንጠቃለል የሚለው ሃሳብ ዛሬ ውሳኔ አግኝቷል።

ከግማሽ ቀን በላይ በወሰደው የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ አስተዳደር ቦርድ የጠራው ጉባኤ ዛሬ ዲሴምበር 15 ቀን 2013 ዓ.ም የተደረገ ሲሆኑ፤ የቤተክርስቲያኑ አባላት በዚህ ጉዳይ ውሳኔ እንዲሰጡ ተደርጎ በጉባኤው ላይ ከተገኙት ውስጥ በአብዛኛው ድምጽ የሰጡ ምዕመናን በገለልተኛነት እንዲቆይ በመምረጣቸው ቤተክርስቲያኑ እስካሁን እንደነበረው በገለልተኛንቱ እንዲቀጥል ተወስኗል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ካህናት ዛሬ ምርጫ እንዳይደረግ ሆኖም ግን የአንድነት ትምህርት እየተሰጠ እንዲቆይ ጥያቄ ማቅረባቸውን ጉባኤው ውስጥ የነበሩ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ ገልጸው አብዛኛው ምእመናን ግን የካህናቱን ሃሳብ ውድቅ እንዳደረገው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በሚኒሶታ የሚገኙ ከ30 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ይህን የውሳኔ ቀን በጉጉት ሲጠብቁት የቆየ ሲሆን ውሳኔውን ለማወቅ ዛሬ ሙሉ ቀን የዘ-ሐበሻ ስልክ ሲጨናነቅ ነበር የዋለው።

በዛሬው ጉባኤ ዙሪያ ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች መረጃ እንዲሰጡልን ለቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ መኳንንት ታዬ ከምሽቱ 6:30 ጀምሮ ስልካቸውን ስንደውል የነበረ ሲሆን ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ሃሳባቸውን ማካተት አልቻልንም። ሆኖም ግን እንዳገኘናቸው የነበረውን ሁኔታ ጠይቀን ለአንባቢዎቻችን እንደምናካፍል ቃል እንገባለን።

7 Comments

  1. Thanks to the Almighty God that did his best deed for those pure innocent Ethiopians. We have go forward also to cleanup all those evil actors not to backfire again this golden victory once and for all form their power and delegation.

  2. የሚኒሶታ መድሃኔ አለም ምእመናንን ወደድኳቸው። ምርጫቸው አሁን ባገር ቤት ሲኖዶስ ስር እንሁን ወይስ ጊዜው አልደረሰም እንቆይ የሚል ነው። የስድ-ተኛው ሲኖዶስ በምርጫው የለም። የጊዜ ጉዳይ ከሆነ ችግር የለውም። ቀስ ብለው ይገባሉ። መጥፎ ነገር ፋርጣዎቹ በከፈቱት ቀዳዳ አገርና ቤተ ክርስቲያንን በሚጎዳ መንገድ መሄድ ነው።

  3. still independent? till when? leaving yourself out of every thing while our church is dying and our sisters and brothers are dying abroad is un-orthodox but time will come soon. stay independent…that make me SICK!

  4. There are two sets of victims in this church; the Ego victims and the Deprived victims/ belongingness and faith.
    The ones that were beneficiaries of Derg systems who lost their perks and aspirations as a result of coup in 1991 but likes to make money in ethiopia but won’t negotiate on their political ego… which is a double standard,
    And their own victims that survived Derg and the current systems and made it out of the country but discouraged and baffled in the political system of the country and its elites political realm; who abandoned politics and sees betterment for ethiopia only through faith and church alone, … lack of diversity.
    In the end of the day, it is much better than victimizing each other like in london and others. It seems the road to nowhere but God, time and reality prevails and heals.
    The problem is people of limited vision and sense of direction in their life who always enjoy divisive status like winners and losers. The decision is a win for both and all so long as what they agreed upon is clear and bridges to the next level of communication to address the root cause of their problems.
    We all are in the hands of God!, Our times are just seconds in history.
    Ethiopia will prevail !

  5. Because it is all about thee money not the glory of God. We are lost generation, liars, ego, prostitute, and a living dead societies. Your eyes see, your ears hear but you can not able to reach the truth.

  6. ፍቅር ያሸንፋል። ከሁሉ የሚበልጠው ፍቅር ነው እንዳአለው ሐዋርያው በመድኃቤዓለም ቤ/ክ ያሸነፈው ፍቅር ነው። በውይይት እና በብዙኃን ድምጽ አምኖ የሐሳብን ልዩነትን ተቀብሎ ስለፍቅር ሲባል የቤተክርስቲያንን አንድነት መጠበቅ ትልቅ አስተዋይነት ነው። ሜኒሶታዎች እግዚአብሔር ይባርካችሁ፤እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ። ወደፊትም የጳጳሳቱ አንድነት እንዲመጣ ጸልዩ፤ የእርቁ ሂደት እንደገና እንዲጀመርም መጎትጎት ያስፈልጋችኃል። መፍትሔው ያለው እዛጋ ነውና።

  7. You are wrong!! even though love shall always prevail at the end, what we witnessed on Sunday was not near love and truth. In fact I was saddened that a full hour and a half was given for two men to stand and preach Politics and herasey of lies. The two research papers (tinatawi tsehuf) were completely different. I was so disapointed that the other side would only bring empty echoes of politics from voa and esat….REALLY?

    and on top of that how can Pastor daniel be a source about our church???really???

    What I clearly saw on Sunday is Ye meskelu guzo, were so many lie so many betrays, so many does and says dispacable lies but at whats amazing is THIS CHURCH WILL FOREVER LIVE. iT LOOKS as if truth has been weakened just because 325 ppl voted, But Truth and love will prevail. Truth can never be weakened by votes. Those poor people came thinking Weyane is about to take there Church, they were told conspiracies that the Sunday school and priests are Weyanes. They were told so many lies and told manupilated truth. Sadly they were not lucky enough to understand the roots of the Gospel and truth given by the presentation we saw first. very sad.

    egziabehere betun yasda….

Comments are closed.

Addis Ababa
Previous Story

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ቀጭን ትዕዛዝ ተላለፈ

Next Story

ያ’ገሬና የኔ – አትክልት አሰፋ (ጋዜጠኛ) – ከቫንኩቨር

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop