ስለሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ፦«የዋህነት ጸባይ እንጂ እምነት አይደለም» – መጽሀፈ ምሳሌ ምዕ 3 ቁ 1

ከጦመልሳን ወንድራስ

«የዋህነት ጸባይ እንጂ እምነት አይደለም»
መጽሀፈ ምሳሌ ምዕ 3 ቁ 1
«ልጄ ሆይ ሕጌን አትርሳ ልብህ ትዛንዜን ይጠብቅ»
ለእዚህ ጽሁፌ መነሻ ያደረኩት June 2, 2013 በሚኒሶታው ደብረሰላም መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደረገው ስብሰባ ላይ ያየሁትን እኔም እምነቴ የሚስማኝን ለመጽፍ ወደድኩ።
ይህ ሀሳብ የእኔ ብቻ እንደሆነ አንባቢያን እንዲረዱልን በማክበር እጠይቃለሁን።
የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በእድሜ አንጋፋ ከሆኑ ሀይማኖቶች አንዱ ብል ማጋነን አይሆንብንም፤ ይህ ሀይማኖት ሳይከለስና ሳይበረዝ የራሱን ህግጋቶችና ደንቦች እየጠበቀ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ ሲሸጋገር እነሆ ዛሬ ያለንበት ጌዜ ላይ ደርሰናል። ሂደቱም ቀላል አልነበረም። ስንት አበው አባቶች አንገታቸውን ሰተውበታል፣ ተሰደውበታል፤ ታሰረውበታል።
ላለፉት 22 አመታት ግን የምናየው የተለየ ሆኖ አግቸዋለሁን ለዚህም እንደማስረጀ ላቅርብ፦
1 የጸሎት አባቶች ከመንፈስ ስራ ይልቅ ጉቦ መዘፈቃቸው
2 ቤተክርስቲያኖቾ ለአልባሌ ንግድ መግባትና መሰማራት (ገብርኤል፤ኡራኤል፤ልደታ) ለምሳሌ መጠጥ ቤት፤ ቻት ቤት፤ ሙዚቃ ቤት ወዘተ።
3 በዋልድባ የሚኖሩ አባቶች ሲደበደቡ የሲኖዶስ አመራር አባሎች ዝም ብለው መመልከታቸው (አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ)
4 ጳጳሱ ሳይ ሞቱ ሃውልት አቁመዋል እንዲፍርስ ታዞ ድፍረቱ ያለው ነፍስ አባት ማየት ተቸግረናል
5 ጳጳሱ በአለ ሲመታቸውን በሸራተን አስረሽ ምችው ሲሉ ሌሎች ቤተክርስቲኖች የጣፍና የሻማ መግዥ አተው እናያለን
6 ጳጳሱ አቀንቃኖች አምጥትው ጉያቸው ስር እስከማስቀመጥ አዋርደዉታል
7 የስላሴ ኮሌጅ መዘጋት
8 የኦርቶዶክስ ምጽመን በጸሎት አባቶች እንዲያፍርና እንዲሸማቀቅ አድርግውታል
9 ከዚህ በፊት የተያዘው ሽምግልና ፈርሶ ገዥው መንግስት የራሱን ስው ሾሟል
ታዲያ በሂደት ያየናቸው ጳጳስ እንደ ብጽጹ አቡነ ተክለሀማኖትና በቅርቡ ህወታቸውን ያለፈውን ጵዉሎስን እንመልከት ማነው ለነፍሱ ያደር ማነው መንጋውን የጠበቀ ፍርዱን ለናንተ እተዋለሁኝ
ይህ በእንዲህ እንዳለ June 2, 2013 በቤተክስቲያን በተደረገዉ ጉባኤ የቤተክርስቲያኑ ቆሞስና አንዳንድ ሰንበት ተማሪዎች ተሰብስበው ይችን ቤተክርስቲያን ወደ አገር ቤት ካለው ሲኖዶስ እንቀላቀል ይሉናል እንግባ ይሉናል ፀሐይ ላይ ያሰጡት ኩታ ይመስል ይሞጉቱናል ይህ ማለት ከላይ የጠቀስዄቸውን ሁሉ አባሳ መደገፍ አይሆንም። ይቺ ቤተክርስቲያን ላለፉት 21 አመት ሕግና ደንብዋን አስጠብቃ የኖረች በአሜርካን ውስጥ ካሉት ቤተክርቲያን ለምሳሌ የምትቀርብ ብል ማጋነን አይሆንም በእዚህም ምንጊዜም እኮራለሁ።
ከሁሉም በላይ የሚገርመኝ የሰንበት ተማሪዎች ነን ባዮች ከላይ የጠቀስኩትን እውነታ እያወቁ ከቆሞሱ ጋር መወገናቸው ብዙ አይገርመኝም በየትኛውም ኦርቶዶስ ቤተክርስቲያን መዘምራን ቄሱ ፊሽካ ናቸው። ቄሱ በፈለገው ጌዜና ቦታ የሚነፋቸው ጡሩንባ ናቸው ቅዱስ ስራውን እየጣሱ ቅዱስ ማሕበር አባል ነኝ ማለት አይገባኝም ቁሞሱ ይህን ቤተክርስቲያን ወደ ሲኖዶስ ከቀላቀሉ ጳጳስ ይሆናሉ ተብለዋል ታዲያ መዘምራን ለእናንተ ምን ቃል ተገባላችሁ ንገሩን ትላንትና ቤተክርስቲያኑን ባለው ሕግና ደንብ መሰረት ስትመሩ የነበራችሁ ዛሬ ወደ እዛ እንግባ የምትሉን ቆሞሱ ቢሆን ለጳጳስነት የሚያበቃ ዕውቀት ልምድ አላቸውን እኔ እስከማቀው ድረስ በውነት፤ዛሬ፤በውነት፤ዛሬ ከማለት በስተቀር በትክክለኛው ወንጌል ሲያስተምሩ አይችሉም።
ለእዚህ ማስረጃ ሆኖ የማቀርበው ወደ ቆሮንጦስ ስዎች ምዕ 12, አንቀጽ 7-10 ምን ይላል
ቆሞሱ እግዜአብሔር በሰጣቸው ሊቅነት ቢያገለግሉ ምናለ የማታ ማታ የነፍስ አባት የሚሆኑት እርሳቸው አልነበሩምን ታዲያ የዚህን ምስኪና የዋሕነት ተጠቅመው መቼ ነው የምትቆርቡት ከማለት በስተቀር እስቲ አስራት በኩራት ስጡ አይሉም ምክኒያቱም አስራቱን ከሰጠ ቤተክርስቲን ሁሉ ለልመና አደባባይ ባልወጣች ነበር።
አሁን በቤተክርስቲናቺን ውስጥ 20% አስራቱን የሰጣል 80% አልገባውም ወይም የፀሎት አባቶች የሚነግሩት አፈታሪክ ነው የስንበት ተማሪዎች ተብየዎቹ ስንቶቻችሁ ናችሁ አስራት የምትከፍሉ ስንቶቻችሁ ናችሁ ለአዲሱ ሕንጻ መዎጮችሁን የከፈላችሁ ስም አልጠራም ሰም ማየት ይቻላል መዝገቡ ይናገራል ዳሩ አልፈርድባችሁም አንዳንዶቻችሁ ቄስ ጭን ስር ስላደጋችሁ የእግዚአብሔርን ክብር ለቄሱ ስታችሀል፤ አንዳዶቻችሁ መዋለንዋይ አማልሎችሀል ይህን እውነት ማንም ሊደፈጥጠው አይችልም። አንዳዶቻችሁ የዕውቀት ማነስ ይታይባቸዋል
ለእዚህም እንደ ምክኒያት የማቀርበው ሲኖዶስ ማለት ምን ማለት ነው(ሕግ ወይም መተዳደሪያ ደንብ)ማለት ሲሆን አስፈፃሜው አካል ደግሞ ቤተክህነት ይባላል ይህ የእኛ ቤተክርስቲያን በአንድ ኢትዮጵያ በአንድ ሲኖዶስ እናምናለን
ይህ ለእኔም ፤ለቆሞሱም፤ ለመዘምራንም፤ ለቦርዱም፤ እናም ለምመኑም ግልጽ መሆን አለበት ከዚህ ውጭ ስለ ህጉ የነገራችሁ ካለ ስህተት ነው።
ከሁሉም በላይ መናገር የምፈልፈው ማንም ሰው ኢየሱስ አላየም ሥራው፤ተአምሩ፤ ሰብስቦናል የምንጠየቀው በምግባራች ነው እንጅ በያዝነው ሀይማኖት አይደለም ይህ ቢሆንማ ኦርቶዶክስ ተለይቶ ሰማያዌ መንግስትን በወረስን ነበር ይህ አፈ ታሪክ ነው።
አንዳንድ የዋህ ምዕመን እዛ ገብተን መታገል አለብን ይላሉ።
«እግር እራስን አያክም« ትግል መሰዋትነትን ይጠይቀል የፀሎት አባቶች የያዙት ልፊያ ነዉ 22 አመት ተላፍተናል ደክሞናል፣ ለእዚህም «የዮሀንስ ወንጌል ምዕ 11 አንቀጵ 40 ማየት በቂ ነው። ወድ የቤተክርስቲያኑ አባላት ይህ የተጋረጠብን አበሳ አስወግደን ቤተክርስቲያናቺን እንጠብቅ« እምነት ሁሌም አልጋ በአልጋ ሆኖ አያቅም» ከእዚህ ትልቅ ጋሬጣ ካላስወገድን ወ ደፊት ለምናስበውና ለተለምነው የቤተክርስቲያኑ ግንባታ አንደርስም። ለእዚህም አንድ ቃል ልጥቀስና ጹሑፌን ላጠቃል።
«የያቆብ መልክት 2 ምዕ2 አንቀጵ 11 እንዲህ ይላል «ወንድሞቼ ሆይ እምነት አለኝ የሚል ሥራ ግን ሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቀመዋል እምነቱ ሊያድነው ይችላልን»
ታዲያ ኦርቶዶክስ ነን የምንል ሁሉ ቤተክርስቲያናቺንን ማዳን ይኖርብናል ይህ ቡና ረከቦት ስር የሚወራ ወሬ አይደለም የልጆቻችሁ የወደፊት ተስፋ የሚያጠፋ ነው
ዠንጀሮ የመቀመጫዋ መላጣ አይታያትም ይህ ካልታየን በእንግሊዚ ያለውን ቤተክርስቲያን በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ፣ በስላሴው ኮሌጅ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ማየት ይቻላል በዚህ ዓለም ስንኖር የምዳኘው በሕግ ነው ለነፍሳችን ግን የምንዳኘው በፈጣሪያችን ብቻ ነው።
አሁንም ቤተክርስቲናችንን ይጠብቃት መሪዎቻን ማስተዋል የስጥ ያልተከለሰና ያልተበረዘ ወንጌል ማስተማር ይጠብቅባቹኃል
እግዚአብሔር አገራችንን ይባርካት
ጦመልሳን ወንድራስ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ህውሃት እያዘናጋን አንዳይሆን! ለህወሃት መዘናጋት በትውልድ ላይ መፍረድ ነው፤ - ገብረ አማኑእል፤

3 Comments

  1. Let the Almighty God turn their heart to the truth and right track. THIS CHURCH SHOULD KEEP AND MAINTAIN ITS INDEPENDENCE UNLESS THE BRUTAL WEYANE REGIME OUSTED WHICH HAS BEEN DEVOTING TO DISINTEGRATE THE COUNTRY AND ORTHODOX CHURCH.

    We have challenge and curb this obstacle and Weyane’s mission.

  2. Abatochachn betekrstiyann yasrekebun chgr sidersbat gelel blew aydelem.Nebsachwn awerardew new.egna gn yehywet meswaetnet lemekfel enkuan zgju balemehon geleltegtegna netn meretn.Maferiya nen. Egiziabher eko ytazebenal egna gn tkkl nen blen enasbalen.yegeleltegna betekrstiyanat mefeter wedefit ye orthodox b/n begleseboch balebetnet lemeyaz tru menged kefach tegbar honoal.ex. London debre Tsyon.enem endantew asb neber gn betekrstiyann eyegodahu endehone slegebagn aquamen qeyrealehu. yante degmo betam yebase now. lebetekrstiyan teqorquari endalhonk tshufh yasabqal. Ebakh yebetekrstiyan afrashoch akal athun. EPRDF neh endatlegn enem endantew sratun betam eqawemalehu.

  3. Stay away from church the church have right ruled by by her own designeted leaders you politician go to fight with in your politics party or community center
    With no awernes of church don’t bark as a dog if the church fathers want be lead by so called kale awady what is the problem? First of all they sapose to rule with kale awady (original) church rule .our fathers that is good start pls don’t mix church and politics woyane is nothing to do with this but you just trying to scare people giving wrong information my advise to you I like your website you give us fresh socal and economic news when you post relegion specially orthodox tewahedo
    News bring the one who has serving as priest or preacher but pls don’t bring yesefer weregna or alubaltegna like the top article tsehafi it’s is baseless accusations what I read on the top pls be protectional.dont confused yewahan
    Me e menan.

Comments are closed.

Share