December 7, 2013
1 min read

ከሳዑዲ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዝ የነበረው አውሮፕላን በኢትዮጵያዊቷ ነብሰጡር ምጥ የተነሳ ተመልሶ አረፈ

(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያዊያኑን ጭኖ ከሳዑዲ አረቢያ መካ የተነሳው አውሮፕላን በውስጡ የከጫነት ኢትዮጵያያን መካከል አንዷ ነብሰጡር ምጥ ላይ በመሆኑ አውሮፕላኑ ተመልሶ የሳዑዲ አረቢያ ጠረፍ ላይ እንዲያርፍ መደረጉን አረብ ኒውስ ዘገበ።

አረብኒውስ በድረገጹ እንዳስነበበው አውሮፕላኑ ከሽሜሲ የስደተኞች መጠለያ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ጭኖ ይጓዝ እንደነበር ገልጾ ነኢማ ከድር እስማኤል የተባለችው ይህችው ኢትዮጵያዊት በምጧ የተነሳ አውሮፕላኑ በጠረፍ ከተማ በጀዛን አውሮፕላን ጣቢያ እንዲያርፍ ከተደረገ በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ወንድ ልጅ በሰላም መገላገሏን ዘግቧል።

ነኢማ ለዜና ምንጮችትናንት አርብ በሰጠችው ቃል ልጇ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ገልጻለች።

የጀዛን ከተማ ሃገረ ገዢ ንጉስ መሃመድ ነስር ለኢትዮጵያዊቷ ጥሩ የህክምና እርዳታ እንድታገኝ አዘው እንደነበር የዘገበው አረብ ኒውስ በሳዑዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ለወገናቸው ለተደረገው የህክምና እርዳታ ምስጋናቸውን ገልጸዋል ብሏል።

Previous Story

ሚኒሶታ መድኃኔዓለም ደብረሰላማችን ፣ ትንሿ ኢትዮጵያ ምትክ አገራችን – ለሰላምና አንድነት የቆሙ ምእመናን ያስተላለፉት ጥሪ

tplf rotten apple 245x300 1
Next Story

ከወያኔ ምን አተረፍን?

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop