April 12, 2020
6 mins read

የኮረና ቫይረስ ስርጭት እና ሰዋዊ ደህንነት በኢትዮጵያ

ታደሰ ብሩ

ሰዋዊ ደህንነት (Human Security) በተለምዶ ከምናውቀው የመንግስት ደህነት (State Security) በጣም ይለያል። ሰዋዊ ደህነነት ሰው-ተኮር እና ሁለገብ እሳቤ ነው። በስፋት የሚታወቁ 7 ዋና ዋና የሰዋዊ ደህንነት ስጋቶች አሉ፤ እነዚህም (1) የኢኮኖሚ ደህነነት፣ (2) የምግብ ደህነነት፣ (3) የጤና ደህነት፣ (4) የተፈጥሮ ከባቢ (environment) ደህነት፣ (5) የግለሰብ ዜጎች (ነዋሪዎች) (personal) ደህነት፣ (6) የማኅበረሰብ (community) እና (7) የፓለቲካ ደህነት ናቸው።

አሁን አገራችንን (ዓለምንም) እያስጨነቀ ያለው የኮረና ቫይረስ ስርጭት የጤና ደህንነት ስጋት ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን የደህንነት ስጋት ለመቅረፍ አቅሙ የቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው። ይህ ጥረት መቀጠል አለበት፤ ከዚህ በፊትም እንገለጽኩት በዚህ ዘመቻ ሁላችንም ከመንግስትን ጎን የመቆም ኃላፊነት አለብን። የመጣብን አደጋ በደካማ የመንግስት አቅም መቋቋም ሊያዳግት ስለሚችል መንግስትን ማጠናከር የጋራ ኃላፊነታችን መሆን ይኖርበታል።

የጤና ደህነት ችግር የጤና ችግር ብቻ ሆኖ አይዘልቅም፤ ሌሎች የደህነት ችግሮችን ይፈጥራል፤ ቀድሞ የነበሩትን የደህንነት ችግሮችንም ሊያባብስ ይችላል። የኮረና ቫይረስ ስርጭት የኢኮኖሚና የምግብ ደህንነታችን ላይ አደጋ እንደሚያመጣ በብዙዎች ዘንድ ግንዛቤ ያለ ይመስለኛል።

የኮረና ቫይረስ ስርጭት ከጤና ችግርነቱ ባሻገር በኢኮኖሚና በምግብ ደህንነታችን ላይ ካልሆነ በስተቀር በሌሎች የደህንነት ዓይነቶች ላይ ስለሚያስከትለው ችግር ሲነገር ግን ብዙም አልሰማሁም፤ ይህ በጣም ያሳስበኛል። እንዲያውም በግልባጩ “የኮረና ቫይረስ ክስተት በማኅበረሰባችን ውስጥ ያለውን መልካምነት አጉልቶ አውጥቷል“ የሚሉ አስተያየቶችን ነው የምሰማው። ይህ በአጭር ጊዜ እውነት ሊሆን ቢችልም ለረዥም ጊዜ ስለመዝለቁ መጠራጠር ይበጃል። የጋራ ችግር መረዳዳትን የሚፈጥር የመሆኑ ያህል የወንጀሎችና የቅራኔዎች ምክንያትም ሊሆን ይችላል።

ተግባራዊ እርምጃዎችን ካልወሰድን የኮረና ቫይረስ ስርጭት በኢኮኖሚና በምግብ ደህነታችን ላይ ከሚያደርሰው አደጋ ባልተናነሰ (ምናልባትም እጅግ በባሰ) ሁኔታ በግለሰብ ዜጎች፣ በማኅበረሰቦቻችን እና በፓለቲካ ደህነታችን ላይ አደጋ ሊያመጣ ይችላል የሚል ስጋት አለኝ።

“የግለሰብ ዜጎች ደህነት” ስል በቅድሚያ የሚታየኝ በተለይ በከተሞች እየተባባሰ የመጣው የተደራጀ ዝርፊያ፣ ህገወጥነት እና ውንብድና ነው፤ በቂ ትኩረት ካልተሰጠው ኮረና ይህን የወንጀል ዓይነት በከፍተኛ መጠን ሊያባብስ ይችላል። “የማኅበረሰብ ደህንነት” ስል በአዕምሮዬ የሚመጣብኝ ”ማንነትን” መሠረት ያደረጉ ግጭቶችን ነው። የኮረና አደጋ በተራዘመ መጠን ዘርንና ሀይማኖትን ሰበብ የሚያደርጉ ግጭቶች ሊባባሱ ይችላሉ፤ እንዲያውም “አገር በቀል” የሽብር ድርጅቶች የሚፈጠሩበት እድል የሰፋ ነው። “የፓለቲካ ደህንነት” ስል የሚታየኝ የፍትህ እጦት፣ የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ እና አፈና ናቸው።

ምን ይደረግ?

የአደጋውን ስፋትና ጥልቀት በዚህ መልክ መረዳት ለመፍትሄ ፍለጋው የመጀመሪያ እርምጃ ነው። ሁለተኛ፤ መንግስት (በተለይ የሰላም ሚኒስትር እና የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት) ሁለገብ የሀገር ደህንነት ጥናት እንዲያደርግ እጠይቃለሁ። ሶስተኛ፤ አሁን በተፈጠረው አጭር “አመቺ” ጊዜ ውስጥ ሀገራዊ እርቅን መፍጠር፤ ለቅራዊዎች መፍቻ ተቋማዊ መፍትዎችን ማበጀት፤ የተደራጀ ውንብድናን የሚቋቋም ማኅበራዊ መስተጋብር መፍጠር ያስፈልጋል። የኮረና ቫይረስ ስርጭት ብዙ ከቆየ አሁን ያለው መልካም ስሜት አይቆይም፤ ስለሆነም መፍጠን ያስፈልጋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop