January 1, 2020
2 mins read

በኢትዮጵያ ከፍተኛው ወርሃዊ የጡረታ አበል ተከፋይ 153 ሺ ብር ሲሆን ዝቅተኛው ደግሞ 1ሺ 258 ብር ነው

80893756 1508994262585250 4896653555168968704 n

በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ የምዝገባና አበል መወሰኛ ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ እምሩ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት ለጡረተኞች የሚከፈለው አጠቃላይ ዓመታዊ ክፍያ ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ዝቅተኛ ወርሀዊ ክፍያ 1ሺ 258 ብር ሲሆን ትልቁ ደግሞ 153 ሺ ይደርሳል ፡፡

ከፍተኛ የጡረታ አበል የሚከፈላቸው ዜጎች ቁጥር አነስተኛ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ ከከፍተኛ ተከፋዮች መካከል ካፕቴኖች ይገኙበታል ብለዋል፡፡

በሀገሪቱ ሰባት መቶ ሀምሳ ሺ የሚደርሱ ጡረተኞች እንደሚገኙና ኤጀንሲው በዓመት ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ የጡረታ አበል እንደሚከፈል የገለጹት ዳይሬክተሩ በአንጻሩ ደግሞ በአመት አስራ ሁለት ቢሊዮን ብር እየተሰበሰበ ነው፡፡

ኤጀንሲው በአራት ዓመት አንድ ጊዜ የጡረታ ማስተካከያ የሚያደርግ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ፤ሆኖም ነባራዊ ሁኔታዎችን በመመልከት እንዳስፈላጊነቱ ማስተካከያ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ዘጠኝ አይነት የማህበራዊ ዋስትና አይነቶች ቢኖሩም በኢትዮጵያ እየተተገበሩ ያሉት ግን አራቱ ብቻ ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ አንደኛ በእድሜ፣ ሁለተኛ በጤና ምክንያት እና ሦስተኛ በስራ ላይ እያሉ በገጠመ ችግር በደራጎት የሚወጡና ባለመብቱ ሲሞት ለተተኪዎች የሚሰጥ፤ እናትና አባት ልጆች እንዲሁም የትዳር አጋርን የሚያካትት መሆናቸውንም አስረድተዋል።

በኃይማኖት ከበደ / ኢፕድ

 

2 Comments

  1. The numbers do not add up .
    The yearly payment budget of Six billion birrs divided by the 750 thousands retirement recipients is equal to eight thousand birrs for each person per year, eight thousand birrs divided by twelve months is six hundred sixty six birrs per month for each of the seven hundred fifty thousand retirees assuming they all get the same amount monthly.
    Also Ethio-Etitrean Badme war disabled volunteer Wedo Zemach fighters are not getting any retirement payments it is concerning.

  2. Gumareit

    6,000,000,000 is the yearly budget which we pay to 750,000 people .
    We don’t pay 750,000 birrs per month to anyone, the highest we pay for one person is 153,000 Birrs per month and the lowest we pay for one person is 1,258 Birrs per month. I hope it is clear for you now.

Comments are closed.

100046
Previous Story

የአዲስ አበባ ከተማ – የከተማዋን ነዋሪ ስነ-ልቦና ፣ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ማዕከልነትን ታሳቢ ያደረገ የፖሊስ ኃይል ያስፈልጋታል

Next Story

የሲቃ መረዋ – ተስፋዬ ሁነኛው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop