February 23, 2019
2 mins read

በአሜሪካ አሌክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑት አቶ መርጊያ ንጉሴ ፍርድ ቤት ቀርበው ጥፋተኛ ተባሉ

በአሜሪካ አሌክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑት አቶ መርጊያ ንጉሴ ትንናት ፍርድ ቤት ቀርበው ጥፋተኛ ተባሉ፡፡

https://youtu.be/9_PNwyW18Qg

የ58 አመቱ አቶ መርጊያ ጥፋተኛ የተባሉት በማጭበርበር የአሜሪካ ዜግነት አግኝተዋል በሚል ነው፡፡ በዛሬው እለት የተሰየመው ፍርድ ቤቱ እንደገለፀው አቶ መርጊያ በቀይ ሽብር ወቅት ተጠርጣሪ እስረኞችን ደብድበዋል፣ ገርፈዋል፣ አሰቃይተዋል፡፡ ይህ ድርጊት የተፈፀመባቸው ግለሰቦችም ለዘላቂ ጉዳት ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡

 

ይሁንና በ1999 እ.ኤ.አ ወደ አሜሪካ በገቡበት ወቅት ለኢምግሬሽን ሰራተኞች ሙሉ በሙሉ ውሸት የሆነ ታሪክ ተናግረው የስደተኝነት ፈቃድ ማግኘታቸውንና በ2008 ደግሞ የአሜሪካ ዜግነት እንደተሰጣቸው ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ ዜግነት ለማግኘት ቃለመጠይቅ በተደረገላቸው ወቅት ማንንም ሰው በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት እንዳላሰቃዩ ተናገረው የነበረ ቢሆንም ለፍርድ ቤቱ ግን ያንን ያሉት በሀሰት እንደነበር አምነዋል፡፡ በአሜሪካ ህግ መሰረት በሀሰት መግለጫ ዜግነት ማግኘት ክልክል በመሆኑም የጥፋተኝነት ውሳኔ እንደተላለፈባው ፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ የአሜሪካ ረዳት ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቤንዝኮወውስኪ እንደተናገሩት ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅመው ራሳቸውን ደብቀው አሜሪካ ለሚኖሩ ሰዎች ምንም ምህረት የሌለ ሲሆን ሌሎች እንደ መርጊያ አይነቶችም ታድነው ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡ አቶ መርጊያ የፊታችን ሜይ 17 ቀን ፍርድ እንደሚሰጣቸው ለመረዳት ችለናል፡፡

94221
Previous Story

አዴፓ በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ጠንካራ አቋም እንዳለው አስታወቀ

94227
Next Story

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተቃዋሚዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop