January 16, 2019
2 mins read

ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው

ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡
https://youtu.be/epx_GOJUaUQ
በሁለቱ ኩባንያዎች መሀከል ስምምነቱ የተፈፀመ ሲሆን የዋይፋይ አገልግሎቱ ሲጀምር በአለም አቀፍና በአገር ውስጥ በረራዎች የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም አለም አቀፍ ንግድ ኦፊሰሩ አቶ ሰይድ አራጋው ለካፒታል ጋዜጣ ሲናገሩ ‹‹ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ስምምነት ከፈፀምን በኋላ ለአገልግሎቱ ሳተላይት የሚያቀርብልን አለም አቀፍ ኩባንያ እያነጋገርን ነው›› ብለዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለም ኢትዮ ቴሌኮም እንደአዲስ ባቋቋመው በዚሁ አለም አቀፍ ንግድ ዲፓርትመንት አማካኝነት ከታዋቂ አፕሊኬሽኖች ጋር እየተደራደረ መሆኑን ኦፊሰሩ አስረድተዋል፡፡ ከእነዚህ አፕሊኬሽኖች መሀከል ፌስቡክና ዋትስ አፕ እንደሚገኙበት አቶ ሰኢድ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮ ቴሌኮም ከ27 አለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የድምፅ አገልግሎትን በተመለከተ ስምምነት የፈፀመ መሆኑን የተናገሩት ኦፊሰሩ በቅርቡ ደግሞ በፊት በነፃ የነበሩት የፌስ ቡክና የዋትስ አፕ የፅሁፍ መልእክቶች ላይ አፕሊኬሽኖቹ እንዲያስከፍሉ ለማድረግ በድርድር ላይ መሆናቸውን ለካፒታል ጋዜጣ አስረድተዋል፡፡

93757
Previous Story

‹‹አሁን የህወሃት ሰራዊት አኩርፏል፡፡ ስራ በማበላሸት ላይ ናቸው፡፡” ኮ/ል ጌታቸው ብርሌ

93779
Next Story

የአሜሪካ እርዳታ በግማሽ ሊቀንስ ነው

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop