January 13, 2019
2 mins read

ከሜቴክ የተነጠቁት የህዳሴ ግድብ ስራዎች ለቻይና ኩባንያዎች ተሰጡ

ከሜቴክ የተነጠቁት የህዳሴው ግድብ የኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ገጠማና ሙከራ፣ እንዲሁም የብረታ ብረት ሥራዎች ለቻይና ኩባንያዎች ተሰጡ፡፡ ሪፖርተር ጋዜጣ ዛሬ እንደዘገበው ስራውን ለመስራት ሀይድሮ ሻንጋይ የተሰኘው ኩባንያ የ77 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=bmsf7vBqDX8
ድርጅቱም ለህዳሴ ግድቡ ስድስት የተርባይን ጀኔሬተሮች ግንባታና የተጓደሉ ዕቃዎችን ለማቅረብ፣ የተከላ፣ የፍተሻና የሙከራ ሥራዎችን ለማከናወን ተስማምቷል፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ እና የቮይት ኃይድሮ ሻንጋይ ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ሚስተር ታንግ ሹ በአዲስ አበባ እንደተፈራረሙ ከመሥሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ እንዳሉት፣ የተጓተተውን የግድቡን ግንባታወደ ቀድሞው ፍጥነት ለመመለስ ከኩባንያው ጋር የተደረገው ስምምነት ወሳኝነት ከዚህ ስምምነት ቀደም ሲልም ፓወር ቻይና ከተሰኘው ኩባንያ ጋር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የኃይድሮሊክ ስቲል ስትራክቸር ግንባታ ለማከናወን፣ የ125.6 ሚሊዮን ዶላር የግንባታ ስምምነት መፈራረሙ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኮንትራት ስምምነቱ የተከናወነው የውኃ መቀበያአሸንዳዎችንና የመቆጣጠሪያ በሮችን፣ እንዲሁም የ11 ኃይል ማመንጫ ተርባይኖችን የዲዛይን፣ የአቅርቦት፣ የገጠማ፣ የፍተሻና የሙከራ ሥራዎች ለማከናወንከኩባንያው ጋር ስምምነት እንደተደረሰ ለማወቅ ተችሏል፡፡

93730
Previous Story

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከፋይናንስ ተቋማት ኃላፊዎችና ተወካዮች ጋር በዘርፉ እየተካሄዱ ባሉ የለውጥ ሂደቶች ዙሪያ ተወያዩ

93736
Next Story

የክፍለ ከተማው ባለስልጣን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ይዘው ተሰወሩ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop